Connect with us

ሀገር ዉስጥ

የዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመዲናዋን የትራንስፖርት ችግሮች የሚያቃልሉና የመንገድ መሰረተ ልማትን ይበልጥ ለማዘመን የሚረዱ የ3 የመንገድ ፕሮጀክቶችን የፊርማ ስነ ስርዓት አከናወነ፡፡

Published

on

የዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመዲናዋን የትራንስፖርት ችግሮች የሚያቃልሉና የመንገድ መሰረተ ልማትን ይበልጥ ለማዘመን የሚረዱ የ3 የመንገድ ፕሮጀክቶችን የፊርማ ስነ ስርዓት አከናወነ፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር 3 ቢሊዮን ብር የሚጠጋ ወጪ የሚደረግባቸዉ በአጠቃላይ ከ10 ኪሎሜትር በላይ ርዝመት እንዲሁም ከ15-30 ሜትር የጎን ስፋት ያላቸዉን 3 የመንገዶችና ድልድይ ፕሮጀክት ግንባታዎችን ሊያከናዉን እንደሆነ አስታወቀ፡፡
ፕሮጀክቶቹ በከተማ አስተዳደሩ በጀትና በአለም ባንክ ብድር የሚከናወኑ መሆናቸዉ ተገልጿል::

የመጀመሪያዉ የአፍሪካ ጎዳና -ኤድናሞል አደባባይ-22ማዞሪያ -እንግሊዝ ኢንባሲ የአስፋልት መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ሰሆን 4.4 ኪሎሜትር እርዝመት እንዳለዉ ተገልጿል፡፡
ከ2.4-4 ሜትር ስፋት ያለዉ የእግረኛ መንገድ ፤2ሜትር ስፋት ያለዉ የብስክሌት ብቻ መሄጃ መንገድ 9የሳይክል ማቆሚያ 3 የሳይክል ማከራያ ቦታዎች እንደሚያካትትና ለከተማዋ የመጀመሪያ የሆነ የመንገድላይ የደህንነት ቁጥጥር ስርአት ያካተተ ዲዛይን መሆኑንም ይፋ ተደርጓል:: ይህንን ስራ የሚሰራዉ ኮንትራክተር የቻይና ሲቪል ኢንጅነሪንግ ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን እንደሆነ ተገልጿል::

ይህ ፕሮጀክትም ከ1.2 ቢሊዮን ብር በላየ እንደሚፈጅ ተገልጿል:: ሁለተኛዉ የየአደር ጤና በለቴ-ሱቅ -አለምገና አደባባይ የአስፋልት መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ነዉ:: አዲስ አበባ ካሏት 5 በሮች መካከል አንዱ እንደመሆኑ መጠን ከተማዋን በዙሪያዋ ካሉት አካባቢዎች በተለይም ከደቡብና ደቡብ ምዕራብ መዉጫ ማለትም ወደአለም ገና ፣ቡታጅራ ፣ሶዶ፣ወልቂጤና ጅማ ለሚደረጉ ጉዞዎች ትልቅ የትራንስፖርት ማሳለጥ እንዲኖር ያደርጋል ተብሏል፡፡

5.6 ኪሎሜትር ርዝመት ያለዉ ሲሆን የእግረኛ መንገድን ጨምሮ 30 ሜትር ስፋት እንደሚኖረዉ ተገልጿል:: ይህንን ስራ የሚሰራዉ ኮንትራክተር ይርጋለም ኮንስትራክሽን ሀ.የተ.የግ.ማ እንደሆነና ከ1.3 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪዉን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እንደሚሸፍን ተገልጿል::
ሶስተኛዉ የአቃቂ ዴልድይ ግንባታ ፕሮጀክት ነዉ:: 61.2 ሜትር ርዝመት ያለዉ ሲሆን 140 ሜትር ወደድልድዩ የሚያገናኙ መንገዶችን እንደሚያካትት እና 25 ሜትር የገን ስፋት እንዳለዉ ይፋ ተደርጓል:: ይህንን ስራ የሚሰራዉ ኮንትራክተር ብሪጅ ኮንስትራክሽን ሀ.የተ.የግ. ማ እንደሆነና 447.2 ሚሊየን ብር በላይ እንደሚፈጅ ተገልጿል፡፡

ሙሉ ወጪዉን የሚሸፍነዉ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እንደሆነም ተገልጿል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንተባና የስራ ኢንተርፕራይዝና ኢንዱስትሪ ቢሮ ሀላፊ አቶ ጃንጥራር አባይ እነዚህ ፕሮጀክቶች በመዲነዋ የሚታየዉን የትራፊክ መጨናነቅ ለመቀነስ አቅም ለመፍጠር የሚያስችሉ ኤንደሆኑና በከተማዉ ሰፊ ፕሮጀክቶችን በመቅረፅ ሊሰራ እንደሚገባ በር አፋች መሆናቸዉን ተናግረዋል።
የአዲስ አበባ መንገዶች ባለስልጣን ሀላፊ ኢንጅነር ሞስ ጥበቡ የሶስቱ መንገዶች ፖሮጀክት ቅድሚያ መሰጠት የማህበረሰቡን ጥያቄ ለመመለስ እንደሆነ ገልፀዉ፠ የዉለታ ፊርማ ስነ-ስርአቱ መከናወኑ የተጀመሩ የመሰረተ ልማቶች በአጭር ጊዜዉስጥ እንደሚጠናቀቁ የክትትልና ቁጥጥር ለማድረግ አመቺ እንዲሆን የተደረገ መሆኑንጠጠቁመዋል።

ምክትል ከንቲባዉ የከተማ አስተዳደሩ ፕሮጀክቶች ተጀምረዉ እንዲቆሙና እንዲደናቀፉ ስለማይፈልግ በተሰጠዉ ጊዜ ዉስጥ በጥራትና በፍጥነት በማጠናቀቅ ለማህበረሰቡ አገልግሎት እንዲሰጡ መመሪያ ሰጥተዋል።

በየክፍለከተማዉ ያሉ የስራ አሰፈፃሚዎች በመንገድ ወሰን ምክንያት ለሚፈጠሩ ችግሮች ከአካባቢዉ ነዋሪዎች ጋር በጋራ በመሆን አፋጣኝ የሆነ የመፍትሄ አቅጣጫ እንዲያስቀምጡ ሀላፊነት ሰጥተዋል። እነዚህ ሶስት ፕሮጀክቶች ተጠናቀዉ ለማህበረሰቡ አገልግሎት ለመስጠት የሁለት አመት ጊዜ እንደሚፈጅባቸዉ ተገልጿል።
ከአፍሪካ ጎዳና – እንግሊዝ ኢንባሲ ፕሮጀክት ሁለት ቦታዎች ላይ ዲጅታል የትራፊክ መቆጣጠሪያና ቅፅበታዊ የአዉቶቡስ መረጃ ማግኛ ስርአቶች ዲዛይኑ ላይ እንደሚያካትት ተጠቁሟል።

በዳኛቸዉ መላኩ

ሀገር ዉስጥ

የከንፈር እና የላንቃ መሰንጠቅ ህጻናት ከመወለዳቸው በፌት የሚከሰት ችግር ሲሆን በእርግዝና ወቅት የህጻኑ/የህጻኗ ከንፈር ወይም ላንቃ ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል ሳይገጥም ሲቀር የሚፈጠር ክፍተት /ስንጥቅ ማለት እንደሆነ የህክምና ባለሙያዎች ያስረዳሉ ።

Published

on

የከንፈር እና የላንቃ መሰንጠቅ ህጻናት ከመወለዳቸው በፌት የሚከሰት ችግር ሲሆን በእርግዝና ወቅት የህጻኑ/የህጻኗ ከንፈር ወይም ላንቃ ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል ሳይገጥም ሲቀር የሚፈጠር ክፍተት /ስንጥቅ ማለት እንደሆነ የህክምና ባለሙያዎች ያስረዳሉ ። በአለማችን ላይ በየአመቱ ከ170.000 በላይ ህጻናት ከከንፈር እና ከላንቃ መሰንጠቅ ጋር ይወለዳሉ ። በአፍሪካ ውስጥም ከ32.000 ህጻናት በላይ በየአመቱ ከዚሁ ችግር ጋር ይወለዳሉ ። እንዲሁም ደግሞ በሃገራችን ኢትዮጵያ በየአመቱ ከ3000 በላይ ህጻናት ከከንፈር እና ላንቃ መሰንጠቅ ጋር ይወለዳሉም ተበሏል። ይህም ህጻናቱ ለአመጋገብ ፣ለአተነፋፈስ እንዲሁም ለአነጋገር እክሎች ያጋልጣቸዋል ነው የተባለው ። ስማየል ትሬን በአለማችን የከንፈር እና የላንቃ መሰንጠቅ ጋር ለተወለዱ ህጻናት የማስተካከያ ቀዶ ጥገና በነፃ የሚሰጥ በጎ አድራጎት ድርጅት ነው ። ስማይል ትሬን ከሰን ኢኮ አርት ፎር ሶሻል ደቨሎፕመንት ጋር በመተባበር “ሙቪንግ ስማይል” የተሰኘ የአስፋልት ላይ ባቡር መሰል መኪና በማዘጋጀት፤ አገር አቀፍ የከንፈር እና ላንቃ መሰንጠቅ የግንዛቤ ማስጨበጫ ጉዞ በይፉ መጀመሩን የሰን ኢኮ አርት ፎር ሶሻል ደቨሎፕመንት ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኤፍሬም በቀለ ተናግረዋል። ከ1999 ጀምሮ በአለማችን ላይ የክንፈር እና የላንቃ መሰንጠቅ ላጋጠማቸው 1.5 ሚሊየን ህጻናት ቀዶ ጥገና በነጻ አድረገዋል ተብሏል ። በኢትዮጵያም ከ 2007 ዓ.ም ጀምሮ ከ32.000 ህጻናት እና ወጣቶች በላይ የነጻ ቀዶ ጥገና ህክምና እና አገልግሎት እየተሰጠ ይገኛልም ነው የተባለው ። ስማይል ትሬን በኢትዮጵያ ከ2007 ጀምሮ ከ32 ሺሕ ህጻናት እና ወጣቶች በላይ የነፃ ቀዶ ጥገና ህክምና እና አገልግሎት መስጠቱን የገለጹት በምስራቅ አፍሪካ የስማይል ትሬን ረዳት ፕሮግራም አስተባባሪ ዶ/ር ቤተል ሙሉጌታ ሲሆኑ፤ ከዚህም በተጨማሪም ድርጅቱ ከከንፈር እና ላንቃ ጋር ተያይዞ ነጻ የጥርስ ህክምና፣ የአመጋገብ ምክር፣ የንግግር ህክምና (speech therapy)፣ የማህበራዊ እና ስነ ልቦናዊ ድጋፍ እና ሌሎችም አገልግሎቶችን የያዘ ኹሉን አቀፍ የአገልግሎቶችን በመስጠት ላይ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ዶ/ር ቤተል አክለውም ስማይል ትሬን በአገር ውስጥ ለሚገኙ የግል እና የመንግስት ሆስፒታሎች እና ሀኪሞች የቀዶ ጥገና ህክምና ስልጠናዎችን በመስጠት ዘላቂ የሆነ መፍትሄዎችን እዚሁ ባሉ የጤና ባለሙያዎች እንዲሰጥ እያደረገ እንደሚገኝም አስረድተዋል። የከንፈር እና የላንቃ መሰንጠቅ ጋር ተያይዞ ችግር ያለባቸው የማህበረሰብ ክፍሎችም፤ ድርጅቱ የነጻ ጥሪ ማዕከል 9889 ላይ በነጻ በመደወል ለህክምናው መመዝገብ፣ መረጃ ማግኘት እና መማር እንደሚችሉ ተገልጿል።
በመቅደላዊት ይግዛው

Continue Reading

ሀገር ዉስጥ

በአዲስ አበባ በክርና ፕላስቲክ ፋብሪካ ላይ በደረሰ የእሳት አደጋ 8 ሚሊየን ብር የሚገመት ንብረት ማዳን እንደተቻለ 2 ሚሊዮን ብር የተገመተ ንብረት መውደሙ ተገለፀ ።

Published

on

በአዲስ አበባ በክርና ፕላስቲክ ፋብሪካ ላይ በደረሰ የእሳት አደጋ 8 ሚሊየን ብር የሚገመት ንብረት ማዳን እንደተቻለ 2 ሚሊዮን ብር የተገመተ ንብረት መውደሙ ተገለፀ ።

በአዲስ አበባ ከተማ ሰኞ ምሽት 1ሰዓት ገደማ በአቃቂ ክፍለ ከተማ ወረዳ 7 ልዩ ቦታዉ ቃሊቲ ኢንደስትሪ መንደር ውስጥ በክርና ፕላስቲክ ፋብሪካ ላይ በደረሰ የእሳት አደጋ 2 ሚሊዮን ብር የተገመተ ንብረት መውደሙን የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አስታውቃል። የደረሰዉን የእሳት አደጋ ለመቆጣጠር ሶስት የአደጋ መቆጣጠር ተሽከርካሪ ሃያ አንድ የአደጋ ጊዜ ሰራተኞች መሰማራታቸውን የኮሚሽኑ የህዝብ ግንኙነት ባለሙያ አቶ ንጋቱ ማሞ ለአዋሽ ሬዲዮ ተናግረዋል።

አደጋውን ለመቆጣጠር ሁለት ሰዓት መፍጀቱን አስታውቀዋል። የእሳት አደጋዉ ተስፋፍቶ አደጋዉ በደረሰበት ፋብሪካ ከዚህ የበለጠ ጉዳት እንዳይደርስና በአካባቢዉ ባሉ ፋብሪካዎች እንዳይዛመት ማድረግ ተችሏል ያሉ ሲሆን ። የአደጋ ጊዜ ሰራተኞቹ ባደረጉት ርብርብም 8 ሚሊየን ብር የሚገመት ንብረት ማዳን እንደተቻለ እና አደጋዉ በሰዉ ላይ ምንም ጉዳት አልደረሰም። የአደጋው የመነሻ ምክንያት በመጣራት ላይ ይገኛል በለዋል ።

በመጨረሻም ባሳለፈነው ቅዳሜና አሁድ በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ 1 እና ወረዳ 12 ክፍቱን በተተወ ዉሀ በአቆረ ጉድጓድ ዉስጥ እድሜያቸዉ 12 እና 25 የሆኑ ታዳጊና ወጣት ህይወታቸዉ ማለፉ ተገልጿል ። በአቃቂ ወረዳ 1 እድሜዉ 25 ዓመት የሆነ ወጣት ወንዝ ዉስጥ ገብቶ ህይወቱ አልፎ ተገኝቷል።

የአደጋ ጊዜ ሰራተኞች አስከሬኑን አዉጥተዉ ለፖሊሰ አስረክበዋል ነው የተባለው ። ሌላኛዉ አደጋ እለተ እሁድ 10 ሰዓት ገደማ በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለከተማ ወረዳ 12 ታዳጊዎች ተቆፍሮ ክፍቱን የተተወና ዉሀ ባቆረ ጉድጓድ ዉስጥ ዋና ለመዋኘት ከሄዱ ሶስት ታዳጊ ተማሪዎች መካከል እድሜዉ 12 ዓመት የሆነው የስድስተኛ ክፍል ተማሪ ታዳጊ ዋና ለመዋኘት ገብቶ ህይወቱ አልፎ ተገኝቷል።

የዚህ ታዳጊ አስከሬን በፍለጋ የተገኘዉ ሰኞ ማለዳ ነዉ። አስከሬኑንም ፖሊስ ተረክቧል። በአዲስ አበባ የሚገኙ ወንዞችና በተለይም ክፍቱን የተተዉ ዉሀ ያቆሩ ጉድጓዶች እየተበራከቱ በመምጣታቸዉ ወላጆች ታዳጊ ልጆቻቸዉ እንዲሁም ወጣቶች በወንዞችና ዉሀ ያቆሩ ጉድጓዶች አካባቢ የሚኖራቸዉን እንቅስቃሴ እንዲያቆሙ ማድረግ ያስፈልጋል። በ2014 ዓ.ም ክፍቱን በተተዉና ወሀ ባቆሩ ጉድጓዶች ዉስጥ እድሜያቸዉ 7 እና 15 የሚገመት ታዳጊዎች በእነዚህ ወሀ ባቆሩ ጉድጓዶች ዉስጥ ገብተዉ ህይወታቸዉን ማጣታቸው የሚታወስ ነው ።

በያዝነዉ በ2015 ዓ.ምም መስከረምና ጥቅምት ወር 3 ታዳጊዎች ህይወታቸዉን አጥተዋል። ችግሩ ረጅም አመታትን ያስቆጠረና እየቀጠለ የመጣ ችግር በመሆኑ ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ እሙን ነው ። እንዲህ ባለዉ አደጋም በየአመቱ በአማካይ 12 ታዳጊዎች ህይወታቸዉን ያጣሉም ተብሏል ።

በመቅደላዊት ይግዛው

Continue Reading

ሀገር ዉስጥ

ኢትዮጵያ ለአለም ገበያ ከምታቀርበው የቡና ምርት ዉስጥ 55 በመቶ የሚሆነዉ ከደረጃ በታች መሆኑ ተገለፀ።

Published

on

ኢትዮጵያ ለአለም ገበያ ከምታቀርበው የቡና ምርት ዉስጥ 55 በመቶ የሚሆነዉ ከደረጃ በታች መሆኑ ተገለፀ።
ለኢትዮጵያ ምጣኔ ሀብት የጀርባ አጥነት ሆኖ እያገለገለ ያለዉ የቡና ምርት ለሀገሪቱ ከፍተኛ የዉጭ ምንዛሬ ከማስከገኘቱ በተጨማሪ ሩብ ለሚሆነዉ የኢትዮጵያ ህዝብ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ መተዳደሪያ እንደሆነ መረጃዎች ያመላክታሉ።
ከስድት ሺህ በላይ የቡና ዝርያ እንዳላት የሚነገርላት ኢትዮጵያ እስካሁን እየተጠቀመችዉ ያለዉ የቡና ዝርያ በጣት የሚቆጠር ብቻ ነዉ ተብሏል ።
ሀገሪቱ ለቆላዉም ለደጋዉም ለወይናደጋዉም ለሶስቱም አይነት የአየር ንብረት ተሰማሚ የሆነ የቡና ዝርያ ቢኖራትም ከዘርፉ ማግኘት የሚገባትን ጥቅም በተለያዩ ምክንያቶች እያገኘች እንደልሆነ የኢትዮጵያ ቡና እና ሻይ በለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ዶክተር አዱኛ ደበላ አንስተዋል።
ለዚህም ማሳይ ደግሞ በዝንድሮው አማት ከተለያዩ አለም ሀገራት ለአለም ገበያ ከቀረበዉ 174 ሚሊዮን በላይ ኬሻ ቡና ኢትዮጵያ ማቀረብ የቻለችዉ 5 ሚሊዮን ብቻ ነዉ ያሉት ዳይሬክተሩ ይህም ካለን የቡና ሀብት እና ተስማሚ የአየር ንብረት አንጻር ሲታይ በእጅጉ የወረደ ነዉ ብለዋል።
ይህም ሀገሪቱ ያላትን ሀብት በአግባቡ አለመጠቀሟ በምጣኔ ሃብቷ ላይ እና በዘርፉ ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ ማሳደሩን ተነግሯል።
ኢትዮጵያ በያመቱ ለአለም ገበያ የምታቀርበዉ ቡና መጠኑ እየጨመረ ቢመጣም ከዉጪ ንግዱ የምናገኘዉ የገቢ መጠን ግን በእጅጉ ወርዷል ብለዋል፡፡
የአለም የቡና ገበያ እና የኢትዮጵያ ቡና ገበያ በምንያክል መልኩ ነዉ እየሄደ ያለዉ ስንል ላደረግነዉ ጥናት የኢትዮጵያ ቡና ተስፋ ሰጪ አይደለም የሚል ግኝት ላይ መድረሳቸዉን ዳይሬክተሩ ተናግራዋል ፡፡
ለዚህም ምክኒያት ደግሞ ኢትዮጵያ በብዛት የምታመርተዉ ቡና ደረጃ አምስት ወይም ሂዉጅ የሚባሉ ቡናዎች በጨረታ እና በኒዎርክ ገበያዎች ላይ የሚሸጡ መሆናቸዉን ተናግረዋል ፡፡
እነዚህ ቡናዎች ደረጃቸዉም እጅግ የወረደ በጫራታ የማይሸጡ ተደራድረን እንኳን ለመሸጥ የማይሆኑ ናቸዉ ሲሉም አከለዋል ፡፡ እነዚህ ቡናዎች በአለም ገብያ ከሚቀርቡ የኢትዮጵያ ቡናዎች 55 በመቶዉ ድርሻ የሚዙ እንደሆኑም ተነግሯል፡፡
ኢትዮጵያ በአለም ገበያ በሰፔሻለለቲ ደረጃ የምትሸጠዉ 15 በመቶ ብቻ ነዉ፡፡ ይህን ችግር ቀርፈን የቡናዎቻችንን ደረጃዎች ማሻሻል ካልቻልን በሚጠበቀዉ ልክ ከዘርፉ የሚገኘዉን የዉጭ ምንዛሬ ማሳደግ ያዳግታል ብላዋል።
የኢትዮጵያ ቡና አሁን ላይ በሶስት የተለያዩ የሰዉ ሰራሽ እና የተፈጥሮ ችግሮች እንደተደቀኑበትም ባለስጣኑ አመላክቷል ፡፡
በዚህም አንደኛ የአለም የቡና ዋጋ መዋዠቅ ሲሆን ይህም አረሶ አደሩ የቡና ዋጋ በቀነሰ ቁጥር ከቡና ምርት ወደ ሌላ ምርቶች ለመግባት ይገደዳል፡፡
በሁለተኛ ደረጃ የአየር ንብረት ለዉጥን እንደችግር ያነሱት ዳይሬክተሩ ኢትዮጵያ በብዛት የምታመርተዉ የአረቢካ ቡና ስለሆነ ይህም የቡና ዝርያ በሙቀት ሰለሚጠቃ የአለም ሙቀት በአንድ ዲግሪ በጨመረ ቁጥር የቡና ምርት ተፈላጊነት በእጅጉ እንደሚቀንስ አመላክተዋል፡፡
በሶስተኛ ደረጃ ደግሞ የሃገሪቱ የደንን መመናመን ለዘርፉ ከፍተኛ ስጋቶች መሆናቸዉ በተግዳሮትነት ተወስቷል፡፡
ያሬድ እንዳሻዉ

Continue Reading

በብዛት የተነበቡ