Connect with us

ማህበራዊ

የኢድ አል አድሀ (አረፋ) በዓል አከባበር ቅንጭብ ታሪክ

Published

on

featured
Photo: Social Media

በእስልምና እምነት ውስጥ በዓመት የሚከበሩ ሁለት ትላልቅ ክብረ በዓላት ያሉ ሲሆን ኢድ አል አድሀ (አረፋ) እና ኢድ አልፈጥር በመባል ይታዋቃሉ፡፡ ከእነዚህ ውስጥ የአረፋ በዓል አከባበር ስንመለከት በእስልምና አምስቱ መሰረቶች አንዱ ከሆነው ከሀጅ ስነ-ስርዓት (የአላህን ቤት ከመዘየር) ጋር የተያያዘ ሲሆን የበዓሉ ስም በእስልማና ታሪክ ትልቅ ቦታ ካለው ከአረፋ ተራራ ጋር የተሳሰረ ነው፡፡ ማለትም የአረፋ ተራራ በመካ አካባቢ ከሚገኙት ተራሮች አንዱ ሲሆን አባታችን አደምና ሃዋ አሏህ እንዳይበሉት ከልክሎአቸው የነበረው ዘር በመብላታቸው አሏህ ተቆጥቶባቸው ከነበሩበት የጀነት ዓለም አስወጥቶ ወደ ምድር ካመጣቸው በኋላ ለብዙ ዘመናት እንዳይገናኙ አራርቆ ካኖራቸው በኋላ አሏህ ታርቆቸው እንዲገናኙ በመፍቀዱ የተገናኙበት ስፍራ (ተራራ) ነው፡፡

በአረፋ ወቅት ከሚከናወኑት ሀይማኖታዊ ተግባራት ውስጥ ዋናዎቹ የሐጅ ስርዓት ማከናወን(ካዕባን) መዘየርና መጠወፍ እንዲሁም ኡዱህያ(ዕርድ) ማድረግ ናቸው፡፡ ኡድህያ(ዕርድ) የሚከናውንበት ምክንያት አሏህ ነብዩላህ ኢብራሂምን ልጃቸው ኢስማኤልን እንዲያርዱት አዝዞአቸው የአሏህን ትዕዛዝ ያለምንም ማመንታት ለመፈጸም ልጃቸውን ለእርድ ሲያዘጋጁ ጅብሪል (አ.ሰ) ከጀነት በግ አምጥቶ እንዲቀይርላቸው ታዘዘ፡፡ ልጁ ሳይታረድ በመቅረቱና አባታችን አደም ከእናታችን ሃዋ ጋር ለብዙ ዘመናት በምድር ላይ ተለያይተው ከኖሩ በኋላ አሏህ እንዲገናኙ በመፍቀዱ ምክንያት የደስታ በዓል ሆኖ በየአመቱ እንዲከበር አድርጎታል፡፡ በዚህም ምክንያት የአረፋ በዓልና የእርድ ስነ-ስርዓት በእስልማና ህግ አንድ በሬ ለሰባት ሰው የሚታረድ ሲሆን የሚታረደው በሬ የተሟላ አካልና ጤናማ ሊሆን ይገባል፡፡ ሌላው አንድ ሰው ካስገባው የቅርጫ ስጋ 1/3 ኛው ለድሃ 1/3ኛው ከጎረቤትና ቤተዘመድ 1/3ኛው ለቤተሰቡ አካፍሎ እንዲጠቀም ሀይማኖታዊ አስተምሮው ያዛል፡፡ ይህ የመተሳሰብና የመረዳዳት ሃይማኖታዊ እሴት በባዓል ወቅት መደረጉ ትልቅ ፋይዳ እንዳለው አባቶች ያስረዳሉ፡፡ የእርዱም ስነ ስርዓት የሚከናወነው በእስልምና እምነት ተከታዮች ዘንድ የሚከናወነው የዒድ ሶላት ከተከናወነ በሀዋላ ፈጣሪን በማመስገን ለሀገር ልማትና እድገት ሰላም እንዲሁም ድህነትን አስመልክቶ ዱአና ምርቃት በማድረግ አባወራዎችና ወጣቶች በተገኙበት ይካሄዳል፡፡

በሁሉም የሃገሪቱ ክፍል የአረፋ በዓል በእስልምና እምነት ተከታዮች ዘንድ ከፍተኛ ግምት ተሰጥቶት በድምቀት ይከበራል፡፡ ለበዓሉ የሚደረገው ዝግጅት በዓሉ ከመድረሱ ቀደም ብለው ባሉት ወራቶች ውስጥ የሚጠናቀቅ ይሆናል፡፡ በዚሁ መሰረት እናቶች ለበዓሉ ማድመቂያ የሚሆኑ ቤት እንዳፈራው ያዘጋጃሉ፣ ሴቶች ልጆቻቸው ደግሞ የመኖሪያ ቤቶችን በማስዋብ፣ የመመገቢያ ቁሶችን በማጽዳትና ሌሎች ለበዓሉ የሚያስፈልጉ ቅድመ መሰናዶዎችን በማሟላት ስራ ይጠመዳሉ፡፡ ልክ እንደ ሴቶቹ ሁሉ ወንዶቹም ለአረፋ በዓል የሚያከናውኗቸው የስራ ድርሻ አላቸው፡፡ ለማገዶ የሚሆን እንጨት ፈልጦ ማዘጋጀት፣ ለእርድ የሚሆን ከብት ማቅረብ በአባቶችና በወንድ ልጆቻቸው የሚከወን ይሆናል፡፡ በመሆኑም የአረፋ በዓል በስራ ምክንያት ተራርቆ የቆየውንም ሙስሊም ቤተሰብ ከያሉበት አሰባስቦ የሚያገናኝም በዓል ነው ለማለት ይቻላል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ የአረፋ በዓል ቀደም ሲል ተጫጭተው የቆዩ የሚሞሸሩበት፣ ሌሎች ትዳር ለመመስረት የትዳር ጓደኛቸውን የሚመርጡበትና በባህሉ መሰረት የሚያጩበትም ጭምር መሆኑን የእምነቱ ተከታይ አባቶች ያስረዳሉ፡፡

ሌላው የአረፋ በዓል ያለው ማህበራዊ ፋይዳ በተጣሉ ሰዎች መሀል እርቀና ሰላም እንዲወርድ የሚያስችል ሃይል እንዳለው ሃይማኖታዊ አስተምሮቶች ያስረዳሉ፡፡ ከበዓሉ በፊት የተቀያየሙ ባልና ሚስት፣ልጅና ወላጅ፣ ጎረቤታሞች እንዲሁም የአንድ ማህበረሰብ ጎሳዎች በተፈጠሩ ያለመግባባቶች ያሉ ችግሮችን በአረፋ ሰሞን “ይቅር” ተባብለው ሰላምን ያወርዳሉ፡፡ ይህ ከተከናወነ በሀዋላ ለበዓሉ የተዘጋጁትን ምግብና መጠጥ አብረው በመብላትና በመጠጣት ይደሰታሉ፡፡ የቤተሰብ ህይወት እንዲሻሻል ምንመደረግ አለበት? የሃገሪቷ ሰላም እንዲሰፍንና በአካባቢው ልማት እንዲስፋፋ በአንድነት ከቤተሰብ እና ከማህበረሰቡ ጋር ይመክራሉ፡፡ የአረፋ በዓል ሙስሊም በሆነው ምእመናን ዘንድ ሁሉ ከፍተኛ ግምት ሰጥቶት የሚከበር በዓል ሲሆን ከመብላትና መጠጣቱ ባሻገር ሌሎች በርከት ያሉ ቤተሰባዊና ማህበራዊ ፋይዳዎች ጭምር ያሉት እንደሆነ ይታወቃል፡፡ በአንዳን አካባቢዎች የእምነቱ አስተምህሮ ባይሆንም የሴቶች አረፋ እየተባለ ከዋናው የዒድ በዓል ዋዜማ የሚከበር በዓል አለ። በዚህ እለት ሴቶች የበዓሉ ቅድመ ዝግጅት ማጠናቀቃቸውን የሚያረጋግጡበት ቀን ነው፡፡
በዳኛቸዉ መላኩ

ሀገር ዉስጥ

ከድንበር ጋር ተያይዘዉ የሚፈጠሩ የፀጥታ ችግሮችን በሰላማዊ መንገድ እየፈታሁ ነዉ ሲል የሲዳማ ብሔራዊ ክልል አስታወቀ ፡፡

Published

on

featured
Photo: Social Media

በኢትዮጵያ በአራቱም መአዘናት ከድንበር ጋር ተያይዞ እና በተለያዩ ምክንያቶች ግጭቶችን መመልከት አዲስ አይደለም ፡፡ በተለይ በድንበር ቅርብ የሆኑ እና በግጦሽ መሬት የሚገናኙ ክልሎች ጋር አንዴ ሞቅ አንዴ ቀዝቀዝ የሚል የድንበር ግጭቶች ይስተዋላሉ ፡፡ ይህን ችግር እና ሌሎች የፀጥታ ችግሮች እንዳይከሰቱ ለማስቻል ጠንካራ የሆነ ስራ እየሰራ መሆኑን የሲዳማ ክልል አስታዉቋል ፡፡ የሲዳማ ክልል ፕሬስ ሰክሬታሪያት ሀላፊ አቶ ፍሊጶስ ናሆም ከጣቢያችን ጋር በነበራቸዉ ቆይታ እንደ ገለፁት በሀገር አቀፍ ደረጃ አሁን ካለዉ ወቅታዊ ሁኔታ አንፃር የሰላም ጉዳይ ትኩረት የሚሰጠዉ ቀዳሚ አጀንዳ ነዉ ያሉት ሃለፊዉ የሲዳማ ክልልም የተለየ የፀጥታ ስጋት ባይታይበትም ግን ጉዳዩን ትኩረት ተሰጦ እየተሰራበት ነዉ ብለዋል ፡፡

ሲዳማ ከኦሮሚያ ክልል ጋር የሚጋራቸዉ ድንበሮች አካባቢ አልፎ አልፎ ከግጦሽ መሬት ጋር የሚያያዝ ግጭት እና የፀጥታ ችግር እንደ ሚከሰት የገለፁት ሀላፊዉ ችግሩ ሳይስፋፋ በህዝብ ለህዝብ ግንኙነት የሚፈታበት መንገድ እየተፈጠረ በመሆኑ እስካሁን የተጀመሩ እና ተጀምረዉ የነበሩ የሰላም ዉይይቶችም በስኬት የተጠናቀቁ ናቸዉ ሲሉ አቶ ፍሊጶስ ለጣቢያችን ተናግረዋል ፡፡ አቶ ፍሊጶስ አክለዉም ሲዳማ ክልል ሞያሌን ጨምሮ ከሌሎች ሌሎች ድንበሮችን በቅርብ እና በርቀት የሚጋራ በመሆኑ ህገ ወጥ የኮንትሮባንድ ንግድን ጨምሮ የሀገርን ሰላም የመነሱ የጦር መሳሪያ ዝዉዉሮች ሊደረጉበት ስለሚችል ከፍተኛ ጥንቃቄ እየተደረገ ነዉ ብለዋል ፡፡

ይህንንም አስተማማኝ ለማድረግ የክልሉ ልዩ ሀይል ከመከላከያ ሳራዊት እና ከፌደራል ፖሊስ ጋር በመቀናጀት የተጠናከረ የኬላ ፍተሻዎች ይደረጋሉ ነዉ ያሉት ፡፡ እንደ ሀገር የሰላም ጉዳይ ትኩረት ተሰጦ ሊሰራበት የሚገባ ጉዳይ ብቻ ሳይሆን የእየለት ተግባር በመሆኑ ሰላም የሌለባቸዉ ብቻ ሳይሆኑ ሳለም ያለባቸዉ ክልሎችም ትኩረት ሰጠዉ ሊሰሩ ይገባል ብለዋል ፡፡
በዮሐንስ አበበ

Continue Reading

ማህበራዊ

በኢትዮጵያ እየታየ ያለዉን የሰላም መደፍረስ ዘላቂ የሆነ መፍትሄ ለመስጠት ሁሉም ማህበረሰብ የሚዳኝበትን ባሀላዊ የግጭት አፈታት ዘዴ አክብሮ መስራት ቢችል ዉጤቱን በቅርብ ጊዜዉስ ማየት እንደሚቻል ተገለፀ::

Published

on

featured
Photo: Social Media

በኢትዮጵያ በሁሉም የሀገሪቱ ክፍል አንዳንድ የፀጥታ መደፍረሶች ከጊዜ ወደጊዜ እየተባባሱ እንደሆነ መረጃዎች በተደጋጋሚ እየወጡ እንደሆነ መረጃዎች ያመላክታሉ:: ይኸንን እና መሰል ችግሮች መፍትሄ ለመስጠት የፌደራል መንግስት የተለያዩ አማራጮችን ሲጠቀም ታይቷል:: ይሁን እንጂ በመንግስት በኩል የተወሰዱት የመፍትሄ ዉሳኔዎች ዉጤታቸዉ ጎልቶ እንዲታይ አላደረገዉም:: በሁሉም የሀገሪቱ ክፍል በተፈጠረዉ የፀጥታ አለመረጋጋት ምክንያት ክቡር የሆነዉ የሰዉልጅ ህይወት ጠፍቷል÷ ዜጎች ለረጅም ዘመናት የካበቱ ንብረት ወድሞባቸዋል እንዲሁም አፈር ፈጭተዉ ዉሀ ተራጭተዉ ካደጉበት ከሞቀ ቀያቸዉ ተፈናቅለዉ ለችግርና ለእንግልት ተጋልጠዋል ::

የተከሰተውን ድርጊት መንግስትና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማቶች አውግዘውታል፡፡ ከነዚህም መካከል የሃገር ሽማግሌዎች ተጠቃሽ ናቸው፡፡ ለችግሩ ዘላቂ መፍትሄ ለመስጠት ጤናና ሰላምን በማስቀደም የሀገር ሽማግሌዎችን በማማከር ሁሉም ማህበረሰብ በሚዳኝበት ባህላዊ የግጭት አፈታት ዘዴ መስራት ቢቻል የሚታየዉን የሰላም መደፍረስ ማስቀረት ይቻላል ሲሉ የአፋር ክልል የሀገር ሽማግሌ የሆኑት አቶ አሊ ያዮለአዋሽ ራድዮ ተናግረዋል :: አቶ አሊ በሀገራችን ሰላም እንዲኖር ከቤተሰቦቻችን ጀምረን መስራት እንዳለብን ተናግረዉ መንግስትና የፖለቲካ ፖርቲዎች ትልቁን ድርሻ ሊወጡ ይገባል ብለዋል:: ባህላይ ትኩረት አድርጎ መስራት ቢቻል የፀጥታ ስጋትና የሰላም መደፍረስ አይታይም ያሉት ደግሞ የአፋር ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ የባህል ሀብቶችና ቅርሶች ጥበቃ ዳይሬክተር አቶ ሀቢብ መሀመድ ናቸዉ::

ዳይሬክተሩ እንደሚሉት የአፋር ክልል ማህበረሰብ የሚዳኝበት የራሱ የሆነ ባህላዊ ህግ ስላለዉ ከአጎራባች ክልል የተፈጠረ ግጭት በስተቀር በክልልሉ የሚኖረዉ የአፋር የማህበረሰብ ክፍል በአሁኑ ሰአት የተስተካከለ የኑሮ ዘይቤ ተከትሎ በሰላም እየኖረ ነዉ ብለዋል:: የሀገር ሽማግሌዎች የሚያቀርቡትን መፍትሄ የፌደራል መንግስቱ በፖለቲካ የአሰራር ስርአትዉስጥ በማስገባት ዉሳኔላይ መድረስ ቢቻልና ባህላዊ የግጭት አፈታት ዘዴን በማጠናከር ማህበረሰቡን በሆነ ባልሆነ ጉዳይ የመሳሪያ አፈሙዝ መዟዟር ማዳን እንደሚቻል አቶ ሀቢብ ጨምረዉ ተናግረዋል:: በኢትዮጵያ በርካታ የሆነዉ የማህበረሰብ ክፍል ግጭት የሚፈታባቸዉ ስርአቶች ቢኖሩም ኢትዮጵያ እስከአሁን በገጠሟትና ባስተናገደቻቸዉ ግጭቶች ላይ ለመፍትሄሰጪነት ሲሳተፉ እምብዛም አይስተዋሉም:: መንግስትና የሚመለከታቸዉ የባለ ድርሻ አካላት ለሚፈጠሩ ግጭቶች መፍትሄ ለመስጠት በሚሰራበት ጊዜ እነዚህን ባህላዊ የግጭት አፈታት ዘዴን ለዘመናት ስንጠቀምባቸዉ ስለኖርን አሁንም ከወቅቱጋር ተዋህደዉ እንዲጓዙ በማድረግ የመፍትሄ መንገድ አድርጓ መዉሰድ ይገባል ሲሉ አስተያየት ሰጪዎቹ ጠቁመዋል::
በዳኛቸዉ መላኩ

Continue Reading

ማህበራዊ

መንግስት የዜጎችን ደህንነት ሊያስጠብቅ ይገባል ሲሉ የህግ ባለሙያዎች አስታወቁ ፡፡

Published

on

featured

ባለፉት ተከታታይ አመታት ማንነት ላይ መሰረት ያደረጉ ግድያዎች በኢትዮጵያ የተለያዩ አካባቢዎች ሲከሰቱ ማየት አዲስ አይደለም ፡፡ ይሁን እንጅ ለሚፈጠሩ ወንጀሎች ሀላፊነት በግልፅ የሚወስድ አካል አለመኖሩ ደግሞ ችግሩን እንቆቅልሽ እንዳ ደረገዉ ከመቆየት ባለፈ ህዝብ መንግስት ላይ አመኔታ እንዳይኖረዉ እያደረገዉ ይገኛል ፡፡ ለዘህም ምክንያቱ ለሚፈጠሩ ጅምላ ግድያዎች የሚወሰደዉ እርምጃ ተመጣጣኝ ባለመሆኑ እንደ ሆነ በርካቶች ሲናገሩ ይደመጣል ፡፡ አለፍ ሲልም ወንጀሎች በተደጋጋሚ በሚፈጠሩባቸዉ አካባቢዎች ላይ በአመራርነት የሚሰሩ ሀላፊዎች ለሚመሩት አካባቢ ሀላፊነት ሲወስዱ አለመስተዋሉ ደግሞ ችግሩን የከፋ እንደደረገዉ ይነገራል ፡፡

ባለዚህም ማሳያ የሚሆነዉ ባለፉት ሁለት ሳምንታት በኦሮሚያ በምእራብ ወለጋ አካባቢ ተደጋጋሚ ማንነት ላይ ያነጣጠረ ግድያ ቤዜጎች ላይ መከሰቱ መንግስት ዜጎችን የመጠበቅ ሀላፊነቱን እየተወጣ ነዉ ወይ የሚሉን ማህበረሰብ ጥያቄ ዉስጥ እንዲገባ እየደረዉ ይገኛል ፡፡ አዋሽ ሬድዮ ያነጋገራቸዉ የህግ ባለሙያዎችም በኢትዮጵያ በተደጋጋሚ የመስተዋለዉን ማንነት ተኮር ግድያን መንግስት ትኩረት ሊሰጠዉ ይገባል ይላሉ ፡፡ ኢትዮጵያ በአለም አቀፍ ደረጃ ተስማምታ በፈረመቻቸዉ ቃል ኪዳኖች እና በህገ መንግስቱ አንቀፅ 13 እሰከ 44 እንደ ተቀመጠዉ የሰዉ ልጅ በየትኛዉም ቦታ በነፃነት መንቀሳቀስ እና ንብረት የማፍራት ብሎም በህይዎት የመኖር መብት አለዉ ተብሎ ተደንግጓል ያሉት የህግ ባለሙያዉ አቶ ካፒታል ክብሬ የተቀመጠዉን መብት የማስከበር ሃላፊነት ደግሞ የመንግስት ነዉ ሲሉ ተናግረዋል ፡፡
በወለጋ አካባቢ የተፈፀሙ ጥቃቶች የሚያሳዩት መንግስት ሀላፊነቱን በአግባቡ አለመወጣቱን በመሆኑ በአካባቢዉ በሃላፊነት ከተቀመጡ አመራሮች አንስቶ እስከ ላይኛዉ እርከን ድረስ መንግስት አጣርቶ ጥፋተኞችን ለፈርድ ማቅረብ እንዳለበት የሚያስገድድ ነዉ ያሉት ደግሞ የህግ ባለሙያዉ አቶ ጥጋቡ ደሳለኝ ናቸዉ ፡፡

የተፈፀመዉ ወንጀል ከሀገር ዉስጥ ህግ በተጨማሪ በአለም አቀፍ ፍርድ ቤቶች ሊያስቀጣም የሚችል በመሆኑ ይህንንም የማድረግ ሀላፊነት ቀጣይ የመንግስት ስራነዉ ብለዋል ፡፡ አቶ ካፒታል አክለዉም በማንኛዉም ሁኔታ የሰዉን ልጅ መብት የተጋፋ እና ህይወት ያጠፋ በወንጀል እንደ ሚያስጠይቅ በህጉ ተቀምጧል ያሉ ሲሆን አሁን እንደሀገር የሚስተዋለዉ ከዚህ ላቅ ያለ ዘዉግ ተኮር የወንጀል ደርጊት በመሆኑ ከመደበኛ የግድያ ወንጀል ባለፈ በከፍተኛ ወንጀል የሚያስጠይቁ ናቸዉ ሲሉ ገልፀዋል ፡፡ ባለሙያዎቹ እንደ ገለፁት በዜጎች ላይ እየደረሰ ያለዉን አሳሳቢ ችግር መንግስት በህገ መንግስቱ በተቀመጠዉ ህግና ደንብ መሰረት የዜጎችን መብት የሚያስከብር በትን መንገድ ሊፈልግ ይገባል ነዉ ያሉት ፡፡

Continue Reading

በብዛት የተነበቡ