Connect with us

ፖለቲካ

የሱዳን የባላደራ መንግስት የሱዳንን ህዝባዊ ቁጣ ያበርደዉ ይሆን?

Published

on

featured

የሱዳን የባላደራ መንግስት የሱዳንን ህዝባዊ ቁጣ ያበርደዉ ይሆን? የአሜሪካ አቋምስ ምንድነዉ?

አልቡርሓን ሰሞኑን ድንገተኛ በተባለለት ሁኔታ የተወሰኑ ሚኒስተሮችንና ሌሎች ባለስልጣናት በማደራጀት ጊዚያዊ መንግስት ወይም ባላደራ መንግስት ማቋቋማቸዉን ተከትሎ የተለያዩ አስተያየቶች እየተሰጡ ነዉ።

የባለ አደራዉን መንግስት ተከትሎ የፖለቲካ ተንታኞች እንደሚሉት ከሆነ የአሜሪካ መንግስት እና የሱዳን መንግስት በጋራ በሰጡት መግለጫ የአሜሪካ መንግሰት እንደደገፈዉ በመግለፅ ላይ ናቸዉ።

ሱዳናዊያን ምሁራን ግን ይህን ሓሳብ አይጋሩትም እንዲያዉም የሱዳን ሉዓላዊ ምክር ቤትና ወታደራዊዉ ክንፍ ሆነዉ መግለጫ መስጠታቸዉ የሚያሳየን ኘገር ቢኖር ሁለቱ አካላት ለፖለቲካ ፓርቲዎች የሚያሳዩት የንቀት መለኪያ ነዉ ሲሉ ይደመድማሉ።

አል ቡርሓን መፈንቀለ መንግስቱን አድርገዉ ሱዳን በርካታ ዉስብስብ ነገሮችን ባሳለፈ በሁለተኛ ወሩ 15 አባላትን ያካተተ የሚኒስትሮች ቡድን ያቋቋሙ ሲሆን እነዚህ አባላት በባላደራነት ሱዳንን ያሻግራሉ የተባሉ ናቸዉ።

የሱዳን ህገ መንግስት አደጋ ላይ እንዳይወድቅ ወሳኝ ነዉ በሚል እነዚህ አዲስ ተሿሚዎች ሱዳንን እስከ ምርጫዉ ድረስ እያስታመሙ ይመሩታል እየተባለም ነዉ።

ግን እዚህ ላይ መነሳት ያለባቸዉ በርካታ ጥያቄዎች አሉ ከእነዚህ መካከል እንደ እሳት ወላፈን የሚያቃጥለዉን ተቃዉሞ ማስቆም ይችላሉ ወይ? ሱዳንን እየፈተነ ያለዉን የኢኮኖሚ ቀዉስ ማስተካከል ይችላሉ ወይ? ጣራ የነካዉን የኑሮ ዉድነቱንስ ማዉረድ ይችላሉ ወይ? በፋብሪካዎች መዘጋት ሳቢያ ሱዳን ዉስጥ የተንሰራፋዉን የስራ አጠሰነት ቁጠሰር መቀነስ ይችላሉ ወይ? የሚሉትን ማንሳት ይቻላል።

የኢኮኖሚ ጉዳዮች ኤክስፐርት የሆኑት ዶር ዓብዱልዓዚም አልሙሐል በዚህ ጉዳይ ሰፋ ያለ አስተያየት ከሰጡት ምሁራን መካከል አንዱ ናቸዉ።

እንደእርሳቸው አገላለፅ ከሆነ ይኸ የባለአደራ መንግስት ስራ ከመጀመሩ በፊት ከወታደራዊዉ ክንፍ እና ከፖለቲካ ፓርቲዎች ተፅእኖ ራሱን ያፀዳ መሆኑን ለሱዳን ህዝብ ማሳየት አለበት ሲሉ ያብራራሉ።

እንደ ዶ/ር ዓብዱልዓዚም አልሙሐል ከሆነ  ይኸ አሁን የተቋቋመዉ የባላደራ መንግስት ሱዳን ዉስጥ መፍትሔ ካጣዉ የፓለቲካ ፉክክር መሳሳብ እና መናቆር ራሱን ማግለል መቻል አለበት ብለዋል።

የባላደራዉ መንግስት ዋነኛ ዓላማ ጣራ ከቀን ወደ ቀን እየናረ የመጣዉን የዶላር ምንዛሬ ማስተካከል ይኖርባቸዋል ይህን ማድረግ ካልቻሉ በእጥፍ የጨመሩትን የፍጆታ እቃዎች ዋጋ መቀነስ አይችሉም ያሉት ዶር አብዱልዓዚም የእነሱ ስራ በእነዚህ ጉዳዮች ላይ ትኩረት ማድረግ እንጅ ፖለቲካዉ አይመለከታቸዉም።

እኔ በበኩሌ ይላሉ ዶር ዓብዱልዓዚም እኔ በበኩሌ የምመርጠዉ ለእነዚህ አዲስ ተመራጭ ባላደራዎች ከባድና ዉስብስብ ሓላፊነት ባይጣልባቸዉ ጥሩ ነዉ ቀለል ያሉ የተቆጠሩ የሚመዘኑ የማህበረሰቡን መሰረታዊ ችግሮች ብቻ ሊፈቱ የሚችሉ ጥቂት ነገሮች ቢሆኑ እመርጣለሁ ይላሉ ዶር ዓብዱልዓዚም።

እዉቁ ሱዳናዊ የፖለቲካ ተንታኝ ጀማል ሮስቶም በበኩሉ የባላደራዉ መንግስት ሱዳን ባልተረጋጋበት እና ዉስብስብ ችግሮች ባሉበት ወቅት እንደመጣ መንግስት ብዙ ፈተናዎች አሉበት ።

ሱዳን ዉስጥ ፖለቲካዉ የሚመራበት ሰነድ የለም፣ ፓርላማ የለም፣ መንግስት ዉስጥ የሚሰራ የፖለቲካ ፓርቲ የለም፣ ሱዳን ዉስጥ እርስ በርስ መተማመን የለም፣ መጠላለፍ እንጅ መደጋገፍ የለም ስለሆነም በዚህ ወቅት ሱዳንን ለማሻገር መሞከር በመርፌ ቀዳዳ እንደ መሹለክ ነዉ።

ከአሰነዚህ ከላይ ከጠቀስናቸዉ ችግሮች በበለጠ ወጣቱ ጠንካራ ጥያቄዎች አሉት ከሁሉም በፊት የወጣቱን ጥያቄ መረዳትና መመለስ ያስፈልጋል።

የባለአደራዉን  መንግስት አልቡርሓን አደራጅተዉ ለሱዳን መፍትሔ ያመጣል ብለዉ ቢያቀርቡትም ከዉስጥም ከዉጭም እዉቅና አለማግኘቱ ደግሞ ሌላ ፈተና ነዉ።

እዉቅና ባለማግኘቱ ድጋፍም የለዉም ድጋፍ ከሌለዉ ደግሞ አንድ እርምጃ ወደፊት መሔድ የማይችል የትም የማይደርስ ተቋም ወይም አደረጃጀት እንዲሆን ያደርገዋል።

እነዚህ አዲስ ተመራጮች ስራቸዉን ለመከወን ባጀት ያስፈልጋቸዋል። አንዳንድ ፕሮጀክቶችን ለማስፈጸም፣ ደመወዝ ለመክፈል፣ እና ሌሎችንም ለማከናወን ባጀት የግድና የግድ ነዉ ግን ከየት ሊመጣ ይችላል? ሲል ጀማል ሮስቶም ይጠይቃል።

እነዚህን ለማሟላት ደግሞ የህዝብ መዋጮን ተማምነዉ ከሆነ በፍፁም የማይታሰብ ነዉ ያሉት ጀማል ሮስቶም የሱዳን ህዝብ አሁን ባለበት ተጨባጭ ሁኔታ ራሱን ድጎማ እና የሚያስፈለገው ህዝብ እንጅ ከእጁ እና ከኑሮዉ ያለፈ ነገር የሌለዉ የተዳከመ ህዝብ ሆኗል ይለናል ጀማል ሮስቶም።

በአፍሪካ ዓለም አቀፍ ዩንቨርስቲ የማህበራዊ ሳይንስ መምህር የሆኑት ዶር ዓብዱናስር በበኩላቸዉ የወታደራዊዉ ክንፍና የሉዓላዊዉ ምክር ቤት የባላደራ መንግስት መስርቻለሁ ሲል ይፋ ያደረገዉ ነገር ለፖለቲካ ፓርቲዎች ያለዉን ንቀት ግልፅ አድርጎ አሳይቶናል ይላሉ።

እንደ እኔ እይታ ከሆነ ይላሉ ዶር ዓብዱናስር እንደ እኔ እይታ ከሆነ ይኸ የባላደራ የሚባል አደረጃጀት አንድ እርምጃ ወደፊት መሄድ የማይችል ነዉ የህዝባዊ አመፁ መቀጠል ፣ ድጋፍ አለማግኘት፣ እዉቅና አለማግኘት፣ የመንገዶች መዘጋት፣ የባጀት አለመኖር፣ የወታደሩ ተፅእኖ እና ሌሎችም ተደማምረዉ የረባ ስራም እንዳይሰራ ያደርጉታል ይላሉ።

ወታደራዊዉ መንግስት ከአሜሪካ የልዑካን ቡድን ጋር ሆነዉ የሰጡት መግለጫ አሜሪካ ለዚህ ለባላደራዉ መንግስት ያላቸዉን ድጋፍ ያሳየ ነዉ ያሉት ደግሞ ሌላኛዉ የፖለቲካ ተንታኝ ዶር አልፋቲህ ዑስማን ናቸዉ።

በእርግጥ ይኸ የባላደራ መንግስት በርካታ ፈተናዎች አሉበት በዉጭ በኩል የአፍሪካ ህብረትን፣ የአዉሮፓ ህብረትን፣ የአሜሪካ መንግስትን፣ የእንግሊዝን፣ የዓለም ባንክን እና የዓለም አቀፍ የገንዘብ ድርጅትን ድጋፍ ማግኘት የግድ ይለዋል።

በሐገር ዉስጥ ደግሞ እንደ ሰደድ እሳት እየተዛመተ ያለዉን የተቃዉሞ ንቅናቄ ለማስቆም በፖለቲካ ፓርቲዎች መካከል ስምምነት እንዲኖር ያላሳለሰ ጥረት ማድረግ ይጠበቅባቸዋል። ይህ ደግሞ አሁን ሱዳን ዉስጥ ባለዉ ተጨባጭ ሁኔታ የህልም እንጀራ ነዉ ይላሉ ዶር አልፋቲህ ዑስማን።

አሁን የተደራጀዉ መንግስት በተንቀሳቃሽ አሸዋ ላይ የሚሄድ መኪና ማለት ነዉ በዛ ላይ ደግሞ እዉቅና የተነፈገዉ መንግስት ነዉ ስለዚህ ከንቱድ ድካም ነዉ ያሉት ደግሞ በልማትና በመልካም አስተዳደር ዙሪያ ምሁር የሆኑት ኡስታዝ ሙሐመድ ዑመር ፈይሰል ናቸዉ።

አልየዉም አልታሊ

ጃንዋሪ 25/2022

Click to comment

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ፖለቲካ

ከመንግስት በተጨማሪ በንጹሃን ዜጎች ለሚደረስዉ ጭፍጨፋ ህዝቡም ተጠያቂ ነዉ አሉ፡

Published

on

featured
Photo: Social Media

በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች በንጹሃን ዜጎች ላይ ለሚደርሰዉ ጭፍጨፋ እና ግድያ ከመንግስት በተጨማሪ ህዝቡም ተጠያቂ መሆን አለበት ብለዋል፡፡
የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስተር አብይ አህመድ ዶ/ር በኢትዮጵያ በተለያዩ አካባቢዎች እና በምዕራብ ወለጋ በንጹሃን ዜጎች ላይ በሄርን ወይንም ማንነትን መሰረት ተደርገዉ ለተፈጸመዉ ግድያ ሀዝቡም ተጠያቂ እንደሆነ በዛሬዉ እለት ከህዝብ ተወካይዎች ምክር ቤት ለቀረቡላቸዉ ጥያቄዎች ምላሽ የሰጡት ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ በንጹሃን ዜጎች ላይ ለሚደርሰዉ ጥቃት መንግስትን ብቻ ተጠያቂ ማድረግ ተገቢነት የለዉም በለዋል፡፡

በሃገሪቱ የሚኖሩ ዜጎችን ደንህነት የማስጠበቅ ሃላፊነት የመንግስት ቀዳሚዉ ሃለፊነት ቢሆንም ህዝቡ እንዲህ አይነት አሰቃቂ ወንጀሎች ሲፈጸሙ መንግስትን ብቻ ተጠያቂ ለማድረግ መሞከርም ተጠያቂ አድርጎ መክሰስ ችግሩን ከመቅረፍ ይልቅ ያባብሰዋል እንጂ መፍቴ ሊያሰገኝ አይችልም ብለዋል፡፡ በያካባቢዉ ችግሮች በተፈጠሩ ቁጥር የመንግስትን መዋቅር ዳር ቆሞ መተቸት ሀገሪቱን አሁን ከ ገባችበት ውጥንውጥ ሊታደጋት አይችልም ችግሩን ማሰዎገድ እና መቅረፍ የምንችለዉ እንደ አንድ ህዝብ አሸባሪዎችን እና የእኩይ አላማ ተባባሪዎችን በትብብር ክንድ መሶገድ ስንችል ብቻ ነዉ ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስተሩ፡፡ ከዚህ ባለፈ ግን መንግስትን እና የጸጥታ አካላትን መወንጀል እና ለንጹሃን ዜጎች ሞት፣መፈናቅል እና ጭፍጨፋ ተጠያቂ ማድረግ የማያሰኬድ መንግድ ከመሆኑ በተጨማሪ በትንሽ ክፍያ ሰለ ሀገራቸዉ በየበረሃዉ ለሚዋደቁ የጽጥታ አካላት የሚከፍሉትን ዋጋ መነፈግም ጭምር ነዉ ብለዋል፡፡

ሰሞኑን በሃገሪቱ አንዳንድ አካባቢዎች በተደረጉ የሰላም መስከበር ሒደት በርካታ የጸጥታ አካላት ከሒወት ማጣት እሰከ ከፍተኛ የአካል ጉዳት መስዋዓትነት ከፍለዋል ብለዋል፡፡
ይህን ሳይረዱ አና ሳያገናዝቡ በጸጥታ አካላት ላይ የሚደረገዉ ስም የማጥፋት ተግባር ተቀባይነት የለዉም ብለዋል፡፡ በሃገሪቱ አሁን ላይ ያለዉን ጦርነት የግራጫ መልክ የያዘ መሆኑንም ያነሱት ጠቅላይ ሚኒስተር በኢትዮጵያ ባለፉት ጥቂት አመታት በንጹሃን ዜጎች ላይ የደረሰዉ ግድያ፣ ጭፍጨፋ እና መፈናቅል ከሌሎች ያደጉ ሀገራት ጋር ሲነጻጸር የሚፈጸሙ ሰብአዊ ጥቃቶች ወይንም ጭፍጨፋዎችን በእጅጉ አናሳ ነዉ ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፡፡

እንዲህ ያሉ የሽብር ተግባራት ወይንም የንጹሃን ጭፍጨፋዎች ፣ግድያዎች እና መፈናቀሎች በየትኛዉም አለም ሀገራት የተለመዱ ናቸዉ ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ይህ ችግር አሁን ላይ የአለም ትልቁ ስጋት ነዉ ብለዋል፡፡ የአሸባሪዎች ጥቃት እንደየ ሀጉራቱ የተለየ ይሁን እንጂ በሁልም አለም ሀገራት የሚፈጸም ሰለመሆኑም አንስተዋል፡፡ በአለም ላይ ካሉ ሃገራት ጠንካራ የደንህነት ተቋማት ካሏቸዉ ሃገራት ዉስጥ አሜሪካ ቀዳሚ መሆኑን ያብራሩት ጠቅላይ ሚኒስትሩ በ 2020 ብቻ በአሜሪካ ከ 20 ሺህ ባላይ ንጹኃን በአሸባሪዎች ተገድለዋል አለያም ሞተዋል ብለዋል ፡፡ ከዚህ በተጨማሪ በአሜሪካ በተለያዩ ግዛቶች ባለፉት ስድስት ወራቶች ቢቻ በሺዎች የሚቆጠሩ ንጹሃን ሰዎች በመሳርያ እንደ ተገደሉም አብይ አህመድ አያይዘዉ አንስተዋል፡፡ ይህም በኢትዮጵያ በንጹሃን ዜጎች ላይ ከሚደርሰዉ ጭፍጨፋ ጋር ሲነጻጸር በእጅጉ ያነሰ እንደሆነ ለምክር ቤቱ አባላት በሰጡት ምላሽ እና እና ማብራርያ ገልጸዋል፡፡
በያሬድ እንዳሻዉ

Continue Reading

ፖለቲካ

ኬኒያ ለመጨረሻ ጊዜ አድርጋው በነበረው ፕሬዝደንታዊ ምርጫ በሀገሪቱ አለ መግባባት መንስኤ

Published

on

Photo: cfr.org

አፍሪካዊያን ወደ ቀልባቸው እየተመለሱ ነው ይላል የብሉምበርጉ ዴቪድ ሄርብሊንግ። ኬኒያ ለመጨረሻ ጊዜ አድርጋው በነበረው ፕሬዝደንታዊ ምርጫ በሀገሪቱ አለ መግባባት ተፈጥሮ ነበር። ይህንንም ተከትሎ በርካታ ኬኒያዊያን ተገደሉ።
ለምስቅልቅሉ መነሻ የሆነው ኬኒያ ባደረገችው ላለፉት አራት ፕሬዝደንታዊ ምርጫዎች ላይ ዕጩ የነበሩት ራኤላ ኦዲንጋ በምርጫው መሳተፍ ነበር። ኦዲንጋ እንደ አውሮፓዊያን አቆጣጠር ኬኒያ ላደረገቻቸው የ 1997፣2007፣2013 እና 2017 ፕሬዝደንታዊ ምርጫ ላይ በዕጩነት ቀርበው ተወዳድረዋል። በመጨረሻ ምርጫ ላይ ዋነኛ የኬኒያታ ተፎካካሪ ሆነው መጡ። ደጋፊዎቻቸውም ቁጥራቸው በእጅጉ ጨመረ።
በምረጡኝ ቅስቀሳ ወቅትም የኦዲንጋ ደጋፊዎች ከከኤኒያታ ደጋፊዎች ጋር እልም ወዳለ ፀብ ውስት ገቡ። የሀገሪቱ የምርጫ ቦርድ ውጤት ካሳወቀ በኋላ የፀቡ አቅጣጫ በደጋፊዎቹ መካከል መሆኑ ቀርቶ በኦዲንጋ ደጋፊዎችና በፖሊስ መካከል ሆነ። ፖሊስም በእጁ ያለውን መሳሪያ ተጠቀመ፤ በርካቶችም ተገደሉ።
ደጋፊዎቻቸውን አነሳስተዋል የተባሉትና በምርጫው መሸነፋቸው የተነገራቸው ራኤላ ኦዲንጋ ወደ እሰር ቤት መወርወር እጣ ፈንታቸው ሆነ።ይህ ሁሉ ከሆነ በኋላ ኝ ከጎረቤት ኬኒያ አዲስ ነገር ተሰምቷልየሆነውን ሁሉ እንዳልሆነ ቆጥረው የሁለቱ ተፎካካሪ ፓርቲዎች መሪዎች እጅ ለእጅ ተጨባብጠው በቀጣዩ የአውሮፓዊያኑ ኦገስት 2022 ላይ ስለሚያደርጉት ፕሬዝደንታዊ ምርጫ ተነጋግረዋል።የአሁኑ የመሪዎቹ ንግግር በምርጫ ውጤት ከተለያየን በኋላልም ቢሆን አንጣጣልም የሚል አንድምታ ይዟል።
የሁለቱ ፓርቲዎች መሪዎች እንዳሉት በምርጫው ውጤት መሰረት ጭምር የመመስረት ዕድል ካገኘን እንዳትጠራጠሩ እናደርገዋለንሲሉ አፍሪካዊያን አይስማሙበትም የሚባለውን የማይደፈርር ሀሳብ ሰንዝረዋል።
ኬኒያ ኦዲንጋን የመሰል ጠንካራ ሀገር ወዳድ ዜጋ ስላላት እንኮራለን ሲሉ ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬኒያታ ተናግረዋል። በቀጣዩ ምርጫ እሱን የመሰለ ፖለቲካዊ ልምድ ያለው ዕጩ በመነኖሩ ኬኒያ ተምሳሌታዊ ምርጫ ታደጋለች ሲሉ የተደመጡት ኬኒያታ፤ድርጅታቸው ጁብሊፓርቲ መንግስት የመመስረት ድምፅ ቢያገኝ እንኳን ኦዲንጋ ሌላ የምርጫ ዘመን ላይጠብቁ በሚኒስትርነት አሊያም በሚፈልጉት የአመራርነት ቦታ ላይ ተመድበው የሚወዷትን ኬኒያ ያገለግላኡ ብለዋል። ይህንን የምናደርገው ኬኒያ ከሁለቱ ፓርቲዎች በላይ ስለሆነች ነው ማለታቸውን ብሉምበርግ አስነብቧል።

በዘመድኩበን ብሩ

Continue Reading

ትኩረት

የአፍሪካ ሀገራት በችግር አረንቋ እንዲገረፉ የሚያደርጋቸው ንግግር ላይ መሰረት ያደረገ የፖለቲካ ምህዳር አለመዳበሩ እንደሆነ ይጠቀሳል፤

Published

on

featured
Photo: Social Media

በአፍሪካ በአራቱም ማዕዘናት የሰላም አየር ከራቃት ዋል አደር ብሏል፡፡ በሁሉም የአፍሪካ ቀጠናዎች ከእርስ በርስ ጦርነት አነስቶ የተፈጥሮ አደጋዎች የአፍሪካ ዜጎችን እንቅልፍ የነሱ ጉዳዮች ሆነዋል፡፡

የተፈጥሮ ችግሮችም ሆነ የእርስ በርስ ጦርነት እጅጉን እያመሳት የምትገኘው ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ እንደሌሎች የቀጠናው ሀገራት ሁሉ ከፍተኛ ችግር ውስጥ መግባቷ እየተገለፀ ይገኛል፡፡

በሀገሪቱ በሰሜናዊ ኬቩ ግዛት ሁሌም የማያባራው ጦርነት ጋብ ሳይል ከሰሞኑ አንድ ከፍተኛ የጤና ባለስልጣን እንዳስታወቁት የፈረንጆቹ አዲስ ዓመት ከገባ ወዲህ ብቻ 730 የሚደርሱ ዜጎች በአስቸጋሪ የኩፍኝ በሽታ መጠቃታቸውን አስታውቀዋል፡፡ በመሆኑም በሀገሪቱ ካለው የጦርነት ቀውስ በዘለለ የበሽታው ስርጭት መፋጠን ለበርካታ ህፃናት ህይወት መቀጠፍም ምክንያት ሊሆን ይችላል የሚል ፍራቻ በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ አረብቧል፡፡

የአለም ጤና ድርጅት በበኩሉ ወረርሽኙ በእጅጉ ህዝቡን እንዳያጠቃ መደበኛ ክትባቶች መሰጠት አለባቸው ያለ ሲሆን የሀገሪቱ የክልል ጤና ቢሮዎች ደግሞ ማዕከላዊ መንግሥቱ አፋጣኝ ርብርብ ሊያደርግ ይገባል ብለዋል፡፡ የአለም ጤና ድርጅት ጨምሮ ባወጣው መረጃም በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ አሁን ላይ 95 በመቶ የሚሆነው ህዝብ ሁለተኛ ደረጃ እድገት ያለው የኩፍኝ ቫይረስ ተጠቅቷል ሲል መረጃውን አስነብቧል፡፡

ታዲያ የዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ነዋሪዎች ካጋጠማቸው ወረርሽኝ በተጨማሪ በየቀኑ በገጠራማ ከተሞች እና አንዳንዴም በዋና ከተማዋ የሚርሱ የታጣቂዎች ጥቃት በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ እንደሆባቸው ይናገራሉ፡፡

የሀገሪቱ ማዕከላዊ መንግሥት እንዳስታወቀው ከሰሞኑ 17 ሰላማዊ ሰዎች በተገደሉበት እና በርካታ ህፃናትና ሴቶች በተጎዱበት ጥቃት የኮንጎ ህብረት ስራ ልማት ወይም እራሳቸውን ኮዲ ኢኮ ብለው የሚጠሩ ታጣቂ ሚሊሻዎች ጥቃቱን አድርሰዋል ብሏል፡፡

የኬቩ ግዛት የደህንነት ተቆጣጣሪ እንደተናገሩት ጥቃቱ የደረሰው በስለት መሳሪያዎች ጭምር ነው ያሉ ሲሆን የግዛቲቱ የሲቪል ማኅበራት ፕሬዝዳት ዣን ሮበርት ባሲሎኮ በበኩላቸው ከተጎዱት መካከል ስድስት ሴቶች ክፉኛ ቆስለዋል ሲሉ ተናግረዋል፡፡

ታዲያ የዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ነዋሪዎች ችግር ያገዘፈው ደግሞ ከመኖሪያ ቀያቸው ተሰደው ወደ መጠለያ ጣቢያዎች ቢገቡም ከሚደርስባቸው ጥቃት ማምለጥ አለመቻላቸው እንደሆነ ስጋታቸውን ደጋግመው ይገልፃሉ፡፡

ለዚህም ማሳያ የሚሆነው በያዝነው የየካቲት ወር መጀመሪያ ሳምንት ላይ በመጠለያ ጣቢያ በደረሰ የታጣቂዎች ጥቃት ከ60 በላይ ዜጎች መገደላቸው ነው፡፡ በመሆኑም በኢቱሪ እና አጎራባች የሰሜኑ ኬቩ አውራጃዎች እየጨመረ የመጣውን ጥቃት ለመቀነስ ካሳለፍነው አመት ግንቦት ወር ጀምሮ ጠንካራ ጥበቃ ቢደረግም ለውጥ ሊመጣ አለመቻሉ በተደጋጋሚ ሲገለፅ ተሰምቷል፡፡

ከሰሞኑም ጥበቃውን ያጠናክራል ተብሎ የታሰበ የዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ የጦር ኃይል ያሳለፍነው ሰኞ ወደ ቦታው ማቅናቱ ተገልጿል፡፡ ነገር ግን መቀመጫቸውን በዋና ከተማዋ ኪንሻሳ ያደረጉ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች እና ፖለቲከኞች በበኩላቸው የጦር ሠራዊትን ማብዛት የዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ሰላም አይመልሰውም ሲሉ ሙግታቸውን ያስቀምጣሉ፡፡

ይሁን እንጂ በኢቱሪ የሚገኘው የሰራዊቱ ቃል አቀባይ ጁ ሊየስ ንጎንጎ የጦር ሰራዊቱን ጥቃት ወደ በዛባቸው ቦታዎች እና የመጠለያ ጣቢያዎች ማስጠጋት የክልሉን ሰላም ያሰፍናል ሲሉ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾችን ኃሣብ ማጣጣላቸው ተነግሯል፡፡

ያለውን ውጥረት ረገብ ያደርጋል በማለትም ባሳለፍነው ሣምንት መጨረሻ ቀናት ላይ የኡጋንዳ ወታደሮች ከዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ የጦር ኃይሎች ጋር በመጣመር የፀጥታ ችግር ወደ አረበበባት ኢቱሪ ግዛት መግባታቸው የሚታወስ ነው፡፡

ሂውማን ራይት ዎች ከሰሞኑ ስለ ሀገሪቱ አጠናሁት ብሎ ባወጣው መረጃ መሠረትም እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር ጥቅምት 2021 ጀምሮ በደረሰ የታጣቂዎች ጥቃትም ሆነ የጎሳ ጥቃቶች ከ40 በላይ ህፃናት፣ 22 ወንዶችና 4 የሚደርሱ ሴቶች በአሰቃቂ ሁኔታ በሀገሪቱ ተገለዋል ሲል ያወጣው መረጃ አመላክቷል፡፡ ታዲያ አጥኚ ቡድኑ እንደገለፀው የጤና ተቋማትን ጨምሮ ከ1 ሺ በላይ ቤቶች ወደ አመድነት መቀየራቸውን አትቷል፡፡

በዲሞክራቲክ ኮንጎ የሂውማን ራይትስ አጥኚ ቶማስ ፌሲ በበኩላቸው በደረሰው ዘግናኝ የዜጎች ግድያ እስካሁን የታጠየቀ የመንግሥት ባለስልጣንም ሆነ የሚሊሻ ታጣቂ አለመኖሩ የአፍሪካ የፍትህ ስርዓት አሁንም የጨለመ መሆኑን የሚያመላክት ነው ሲሉ አስተያየታቸውን መስጠታቸውን አናዶሉ አስነብቧል፡፡

በተጨማሪም የአለም ጤና ድርጅት ባወጣው መረጃም ስለፒንግ ሲክነስ ወይም የእንቅልፍ በሽታ ብሎ የሰየመው ተላላፊ በሽታ ከሰሀራ በታች ባሉ 36 የአፍሪካ ሀገራት ላይ በስፋት እንደሚገኝ ያተተ ሲሆን በዚህኛው የችግር ጅራፍ የበዛባት ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ደግሞ 85 በመቶ የሚሆኑ ዜጎች በዚሁ በሽታ እየተጠቁ ነው ብሏል፡፡ ታዲያ ችግሩን የከፋ የሚያደርገው ይህ ወረርሽኝ በፀፀ ፍላይ ወይም በራሪ ትንኝ መሰል ነፍሳት ከሰው ወደ ሰው መተላለፍ እንደሆነ ተገልጿል፡፡

በመሆኑም ከሰው ሰራሽ ችግሮች እስከ ተፈጥሯዊ ችግር ድረስ እየተፊራረቁ ያደቀቋት የዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ መንግሥት እስካሁን ስለ ሀገሪቱ ተጎዳኝ ችግር ያለው ነገር አለመኖሩ አግራሞትን አጭሯል፡፡ ታዲያ እንደዚህ ዓይነት ተደራራቢ ችግር ሲመጡ ዝምታን በመምረጥ አይተው እንዳላዩ ሆኖ ማለፍ በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ መሪዎች ብቻ የተጀመረ ሳይሆን የመላው አፍሪካ መሪዎች የሰርክ ተግባር መሆኑ ችግሩን ግዘፍ የነሳ ያደርገዋል፡፡

ይህ ችግር ደግሞ  የባሰ ሌላ ችግር እንዲወልድ መንገድ መቅደድ እንደሆነ አፍሪካውያን መሪዎች ሊገነዘቡት ይገባል፡፡ ታዲያ በአራቱም መአዘን ያሉ አፍሪካ ሀገራት በችግር አረንቋ እንዲገረፉ የሚያደርጋቸው ሰላማዊ የሆነ የመንግሥት አደረጃጀት አለመኖሩ እና ንግግር ላይ መሰረት ያደረገ የፖለቲካ ምዳር አለመዳበሩ እንሆነ ይጠቀሳል፡፡

ለዚህም አንዷ ማሳያ የምትሆነው ባለፈው አንድ አመት በጦርነት አረር እየተገረፈች የምትገኘው የኛዋ ኢትዮጵያ ማሳያ ናት፡፡ ታዲያ ይህ የጦርነት አረር የኋላ ኋላ የተፈጥሮ ቀውስ ይዞ እንደሚመጣም በኛው ሀገር የተለያዩ ክልሎች እየታየ የሚገኘው ድርቅ ማሳያ ሊሆን ይችላል፡፡

ትንታኔ ዘገባውን ስናዘጋጅ በዋቢነት አናዶሉን አልጀዚራና ሂውማን ራይትስ ዎች ድረ-ገፅን ተጠቅመናል፡፡

በዮሐንስ አበበ

Continue Reading

በብዛት የተነበቡ