Connect with us

ትኩረት

አፍሪካ አህጉር የምለም ደሃ መሆን ሚስጥር

Published

on

featured
Photo: Getty

አፍሪካ አህጉር ለምለም ነገር ግን ደሀ እናት ናት፡፡ ክንፍ እያላት የማትበር ፔንግዮን ወፍ የሚሏትም አሉ፡፡

ለድህነቷ ምክንያቱ የለምለምነቷ የሚፈጥረው የውስጥና የውጭ ጠላት መሆኑን መስማት ደግሞ ለነዋሪዎቿ ያማል፡፡

አፍሪካ ከድህነቷ መላቀቅ ያልቻለችው ተቆርቋሪ ልጆችና መሪዎችን አለማፍራቷ መሆኑን መስማት የተለመደ ሲሆን የነቁ መሪዎች ብቅ ሲሉ በውጭ ሴራና በውስጥ አመፃ ብዙም ሳይቆዩ ሲጠፉ መታየቱ ደግሞ ሌላ ህመም ነው፡፡

እንግዲህ የውስጥ አምባገነኖችና የግላቸውን ፍላጎት ብቻ የሚያስቀድሙ የጎበዝ አለቆችን መሻትና የነጮች ዘመንን የተሻገረ ወረራና ሴራ አፍሪካን እያላት ደሀ አድርጓታል፡፡

ህዝቦቿ በጦርነት፣ በድህነት፣ በርሀብና በስደት አረር እየተለበለቡ ቀጥለዋል፡፡

በአሁኑ ዘመን እንኳን በየዓመቱ ከአንድ እና ከሁለት በላይ መፈንቅለ መንግሥቶች በአህጉረ አፍሪካ እየተካሄዱ ህዝቦች ለስቃይና እንግልት መዳረጋቸው የተለመደ ባህል ነው፡፡

በያዝነው አመት ብቻ በአፍሪካ አምስት መፈንቅለ መንግሥቶች መካሄዳቸውን ልብ ይለዋል፡፡

መፈንቅለ መንግሥቱ ባልተካሄደባቸው ሌሎች ሀገራትም ጦርነትና ርሀቡ አለ፤ ሽብርተኝነትና ዝርፊያውም ቦታውን አለቀቀቀም፤ ሙሰኝነትና አምባገነንነቱ የሰዎችን ተፈጥሯዊ መብት እንደነፈገ በሌላ ጥግ ቀጥሏል፤ እዳና ብድሩም ባለበት አለ፡፡

ከዚህ በተጨማሪም ድርቅና ጠኔው፣ ቁርና እርዛቱ የሚለበልባቸው የለምለም ራቁት ሀገራት በብዛት የሚታይባት አህጉር ናት አፍሪካ፡፡

የድህረ ቅኝ አገዛዝ አዝማሚያውም ከሰሜን እስከ ደቡብ፣ ከምሥራቅ እስከ ደቡብ የአፍሪካ አሀገራት ውሰጥ ውስጡን እንደ እሾህ እየተተከለና እንደ ባሩድ ጭስ እያጠናት ይገኛል፡፡

መዘርዘሩ ካልሰለቸ የአፍሪካ ጉድ ብዙ ነው፡፡

ታዲያ ሁኔታውን በቋሚነት ለመለወጥ ታስቦ የታቀደ ዘዴ እንዳለ ይታወቃል፡፡ አጀንዳ 2063 ይሰኛል፡፡

የአፍሪካ ኅብረት ያስቀመጠው ባለ 7 ግብ እቅዱ ሰላምና ብልፅግናን፣ አንድነትና ትስስርን ለማስፈን የተቀመጠ ነው፡፡

እቅዱ ሁሉም የአፍሪካ ሰው በልቶ እንዲያድር እና ከድህነት እንዲላቀቅ ከማለሙ በተጨማሪ በአህጉሪቱ ምንም ዓይነት የጠመንጃ ድምፅ እንዳይሰማም አቅዷል፡፡

ይህ እቅድ ለዚህች አመለኛ አህጉር በጣም የተራቀቀና የራቀ የሚመስል ነው፡፡ በብርቱ ከተሰራበት ግን የማይደረስበት ተምኔት አለመሆኑን ዘርፉን የሚያጠኑ ሊኅቂን ይናገራሉ፡፡

ጥያቄው ግን ሀገራቱ በሚጠበቀው ልክ እየሰሩ ነው ወይ? የሚለው ይሆናል፡፡

ሠላሳ ዓመት ለቀረው ለዚህ ትልቅ ግብ ሩጫው ከዚያ በሚያደርስ ፍጥነት ተጀምሯል ወይ? የሚል ጥያቄም ማንሳት ይቻላል፡፡

የዛሬው የአዋሽ ትኩረታችን ተግዳሮቶችና መልካም እድሎችን እንዴት ማየት ይቻላል ሲል የዓለምዓቀፍ ፖለቲካ አጥኚ ሙሁራንን አነጋግሯል፡፡

ወርቁ ያዕቆብ (ዶ/ር) የእስትራቴጂካዊ ጉዳዮች ዓለምአቀፍ ግንኙነትና ዲፕሎማሲ ከፍተኛ ተመራማሪ ናቸው እሳቸው እንደሚሉት ከሆነ እቅዶች ጥሩ ናቸው ነገር ግን እቅዶቹ በሚሳኩበት ደረጃ ሲሰራ እያየን አይደለም የሚለውን ተናግረው ርብርቦች እንደሚያስፈልጉ ይጠቁማሉ፡፡

ዶ/ር ወርቁ አክለውም ሰሞኑን የተካሄደው 35ተኛው የአፍሪካ የመሪዎች ጉባዔ እንኳን ተሰበሰቡ ሲባል ከመስማታችን ውጭ ምን እንዳቀዱ፣ በምን በምን ጉዳዮች ዙሪያ ስምምነት ላይ እንደደረሱ ሲገልፁ አላየንም ይላሉ፡፡

መሰባሰቡ ብቻ ለውጥ እንደማያመጣ የሚናገሩት ሙሁሩ አጀንዳ 2063 እንዲሳካ ከተፈለገ ከፍተኛ ሥራ ይጠይቃል ብለዋል፡፡

ሌላው የዓለምአቀፍ ግንኙነትና ዲፕሎማሲ አጥኚ ሐብታሙ ገ/መድህን በአፍሪካ አህጉር ያለው መፈንቅለ መንግሥት፣ የእርስ በርስ ግጭት፣ የተፋዘዘ ኢኮኖሚያዊ እድገት፣ የህብረቱ ውሣኔዎች አስፈፃሚ ማጣትና የውጮች ጣልቃ ገብነት ካልተቀረፈ አጀንዳ 2063ትን ማሳካት ይከብዳል ሲሉ ጠቁመዋል፡፡

ኢትዮጵያ አጀንዳ 2063ትን የሀገር ውስጥ እቅዷ አካል አድርጋ እየተንቀሳቀሰች እንደሆነ የተናገሩት አቶ ሐብታሙ ሌሎች የአፍሪካ ሀገራት የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የልማት ግብን እቅድ ከማድረጋቸው ውጭ የራሳቸው አህጉር እቅድ በውስጣቸው የልማት ፖሊሲ ሲያካትቱት አይስተዋልም ይህ ደግሞ አንዱ የታለመውን እንዳይሳካ የሚያደርገው ነው፡፡

ስለሆነም ሀገራት የውስጣቸውን እድገት ቅድሚያ ሰጥተው መስራት አለባቸው፤ አጠቃላይ ድምሩም ከዚያ የሚወጣ ነው ሲሉ ገልፀዋል፡፡

በኮተቤ ሜትሮ ፖሊታን ዩኒቨርስቲ የዓለምአቀፍ ግንኙነትና ፖለቲካል ሣይንስ መምህሩ አሰፋ አዳነ (ዶ/ር) የታለመው አጀንዳ 2063 እንዲሳካ ሀገራት የውስጥ ሰላማቸውን ማስፈንና የነጮችን ጣልቃ ገብነት በፅኑ መከላከልና ማስቆም ይጠበቅባቸዋል ብለዋል፡፡

አጀንዳ 2063 ተሳክቶ አፍሪካ እንደታሰበው የበለፀገችና የጥይት ድምፅ የማይሰማባት እንድትሆን የውስጥ ሰላምና እድገትን ማፋጠን ከዚያ አልፎም የነጮችን ጣልቃ ገብነት መቃወም ያስፈልጋል የሚለው የሁሉም ሙሁራን ኃሣብ ነው፡፡

በያለው አዛናው

Click to comment

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ትኩረት

ሩሲያ በዩክሬን የጀመረችውን ወታደራዊ ዘመቻ ተከትሎ የተላለፉ ዉሳኔዎች

Published

on

featured
Photo: Social Media

ዓለማችን ከፌብሩዋሪ 24/2022_ማርች 24/2022 በነበሩት ጊዜያት30 ቀናት ከባዱን ጊዜ አልፋለች። ሩሲያ በዩክሬን የጀመረችውን ወታደራዊ ዘመቻ ተከትሎ ከባድ ውሳኔዎች ተላልፈዋል። አብዛኞቹ ውሳኔዎች ሩሲያን በመቃወም፤ ዩክሬን በመደገፍ የተሰጡ ናቸው። በሩሲያ በኩል የተላለፉት ደግሞ በተቀራኒው። ይሁንና እነዚህ የሁለቱ ወገን የፍቃድና ክልከላ እወጃዎች በዓለም ላይ ላሉ፤ ጦርነቱ በምንም መልኩ የማይመለከታቸው ዜጎች አቅም እየፈተነ ነው። በጦርነቱ መጀመሪያ ሰሞን በጉዞ እገዳዎች የጀመረው የማእቀብ እርምጃ እምብዛም ስጋት ያጫረ አልነበረም። ሁኔታው ቀስ በቀስ ወደ ንግድ ነዳጅ ጉዳዮች ሊያመራ ዓለም የገበያ እንቅስቃሴ በፍጥነት አናግቷል።

በዚህ የአንድ ወር ወታደራዊ ዘመቻ በመጀመሪያ ሁሉም ነገር ይመለከተኛል የምትለው አሜሪካ 100 በሚሆኑ የሩሲያ ባለስልጣናትና የቀድሞዋ ሶቬት ቅራት ያለቻችቸው ግለሰቦች ላይ ማዕቀብ ጣለጭቀጥሎም እንግሊዝንና የአውሮፓ ህብረትን ያስከተለችው ዋሺግተን የጉዞ ታጋቾች ቁጥር ወደ 386 ሰዎች ከፍ አደረጉ። በዚህ እቀባ የቀድሞዎቹ ፕሬዝዳንትና መከላከያ ሚኒስቴር ዪሜትሪ ሜድቬዬቭና ሰርጌ ሸጉ ተጠቃለሉ። ከግለሰብ ወደ ግዢ ልውውጥ ያደረገው ማዕቀብ ብሪታኒያና የአ.ሕ. በጋራ በመሆን ለሩሲያ የሚያቀርቧቸውን ውድ ዕቃዎች አንሸጥም ሲሉ አወጁ። እኛ ያመረትናቸው ተሽከርካሪዎች ሳይቀሩ ሩሲያ ምድር አይሄዱም ሲሉ ወሰኑ።

ካናዳና ጃፓን የማዕቀብ መጣሉን ተግባር ተቀላቀሉ። እንዲህ ከሆነ ያዋጣል ያሉት ፕሬዚዳንት ጆ ባይደን ከእንግዲህ ከሩሲያ የማስገባው ነዳጅ አልፈልግም ሲሉ ከባድ ውሳኔ አሳልፈዋል። ይህ የሆነው ጦርነቱ ተፋፍሞ በወሩ ወገብ ላይ በነበረበት ጊዜ ነው። ከዚህም በኋላ አሜሪካ ሩሲያን በማዕቀብ የሚጫንና ጦርነቱ የሚያወግዝ አጋር ፍለጋ በወሩ ውስጥ በርካታ ሀገራት አካላለች አላደርስ ያላቸውንም ቦታ ስልክ በመምታት “እህ ምን ትላላችሁ “ስትል በሚስጥርም በግልፅም ጠይቃለች። ከሩሲያ ዩክሬወን ጦርነት በኋላ እንደ አሜሪካ እጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አንቶኒዮ ብሊንከን ስራ የበዛበት ባለስልጣን የለም።አሜሪካ አውጋዥና አጋዥ ፍለጋ በአፍሪካ ፣በኤዢያና መካከለኛው ምስራቅ ያደረገችውን ጉዞ የመሩት ብሊንከን ናቸው። ይሁናና ጉዞዋቸው ውቴታማ አልነበረም። አንዳንዶቹ “አንደግፍም”ከሚለው አሉታዊ ምላሽ ያለፈ ማብራሪያ መስጠታቸው የአሜሪካ የዲፕሎማሲ ስራ የቁልቁለት መንገድ ጀምራለች እስከማለት አድርሷቸው ዋል።

የፓክስታኑ ፕሬዚዳንት ኢምራን ካሀን የሰጡት ምላሽ በአንድ ወር ውስጥ በጦርነቱ ጡዘለት ልክ ዓልምን ጉድ ያስባለ ነበር።አሜሪካ በተዓ.ኤስ በሳውዲ አረቢያና ህንድ ጠብቀው የነበረ በጎ ምላሽን ሳታገኝ ቀርታለች። በኪሳራ ወደ ሀገር ቤት የተመለሱትን ብሊንከንናሳርፈው ወደ ኳታር ያቀኑት ፕሬዚዳንቱም ቢሆኑ ከዶሀ መንግስት የተመቸውን ድጋፍ ይዘው አልመጡም። ጦርነቱን ሰእብ አድርጎ ሩሲያን ከዓለም የመነጠሉ ተግባር ብዙ ተደክሞበታል። ሆኖም ውጤቱ አመርቂ አልሆነም ልለዋሺግተን። ዝምታን የመረጡት ሀገራት ከሩሲያ ላለ መቀያየም ነው ቢባልም ነገሩ ግን የዋሽግተን የክሽፈት ጉዞ አድርገው የቆጠሩም ነበሩ። ድሀና ባለ እዳ ሀገራት ባለባቸው ድክመት እየተስፈራሩ በነገሩ ላይ ኧጃቸውን እንዲነከሩ ተጠይቀዋል ፣ተገደዋል። ሆኖም በዝምታ ሽሽታቸው ቀጥለዋል።

በተለይ አፍሪካዊያን የኬቭ ነዋሪዎቻቸው ትኩረት ይሰጣቸው ለሚልለው ጥያቄያቸው መልስ ሳይሰጥ ነገሩን እንዲያወግዙ ሲወተወቱ ሰንብተዋል። በአንድ ወርጦርነት አስገራሚ ተብሎ ከተነሳው ውስጥ ይኸው የአፍሪካዊያን ስደተኞች ጉዳይ ነበር። በጦርነት ውስጥያሉት ዩክሬናዊያን በአፍሪካዊያን ላይ ያደረሱት ግፍ ከአሁግሪቱ የነጠላቸው ይመስላል።በዚህ ረገድ ስኬታማ ተደርጋ የምትወሰደው ዲ.ሪ.ኮንጎ ናት። ብራዚል 223 የኬብ ነዋሪዎች ወደ ፈረንሳይ አሸሽታለች። በማዕቀብ መጣሉ አሜሪካንን የደገፏት የአውሮፓ ሀገራትን ያስደነገተ ውሳኔ ከአውሮፓ ተሰማ። አውሮፓዊያን ከዚህ በኋላ ከሩሲያ አንድ በርሚል አያገኑም ስትል ሩሲያ በግሏ ማዕቀብ ጣለች። ይሄኔ በዓለማችን ከነዳጅ አምራች ሀገራት ቀዳሚ የሆነችው አሜሪካ ሩሲያ በመቃወም የደገፏትን አጋሮች አላየሁም አልሰማሁም በሚመስል ዝም ብሏቸዋል።

የአሜሪካንን ዝምታ ያስተዋሉ ት አውሮፓዊያን ሩሲያ የከለከለቻቸውን የነዳጅ ክፍተር ለመድፈን መካከለኛው ምስራቅ ደጋግመውና ተፈራርቀው ጎበኙት። አፍሪካንም የነዳጅ ፍላጎታቸውን ለማሟላት ደጋግመው ተማፅነዋታል። የፈረሳዩ ኢማኑኤል ማክሮን ፤የእንግሊዙ ቦሪስ ጆንሰን፤ የጀርመኑ ቻንስለር አለፍ ስሆልዝ አውሮፓን ወክለው ነዳጅ ፍለጋ ቢሮዋቸው ትተው የተንከራተቱ መሪዎች ናቸው። በዚህ ፍለጋቸው ከድርጀት ኦፔከን ፣ከመግስታን አልጄሪያን፣ሞሮኮን፣ ናይጄሪያን፣ከአፍሪካ ይናገሩ ሲሆን ከመካከለኛው ምስራቅ ነዳጅ አምራቾች ደግሞ ኩዌትን፣ ሳውዲ አረቢያ ፣ እና ሌሎችንም አግኝተው የነዳጅ ሽጡልን ጥያቄያቸውን አቅርበዋል። ሆኖም አረቦች ከድርጅታቸው ኦፔክ መመሪያ አንወጣም በማለት የተናጠል መልስ ከመስጠት ተቆጥበዋል። አፍሪካዊያን ደግሞ የነዳጅ መሰረተ ልማታችን ደካማ ነው፤እሱን የምታለሙ ከሆነ ነዳጅስ ነበረን ሲሉ በቅድመ ሁኔታ ተለያይተዋል።

አውሮፓዊያን ከሩሲያ የሚገኙት የነዳጅ አቅርቦታቸው ተቋርጦባቸዋል። ከዚህ ውጪ ራሳቸው ባስቀመጡት እገዳና ሩሲያ በሰጠችው ምላሽ ውስጥ ሀገራት ብቻ ከ150 ቢሊየን ዶላር በላይ በአንድ ወር ውስጥ አተውታል። ይህንን በፍጥነት የተገነዘቡት የህብረቱ አባል ሀገራት አካሄዳቸውን ቁጥብ አድርገዋል። ነገሩ ከረገበ በሚል ለማደራደር ሙከራ ያደረጉም ነበሩ። በወሩ ማብቂያ በህብረቱ የአባልነት ቦታ አገኛለሁ በሚል ምኞት ከኔቶ ጎን መሆኗን ያወጀችው ሞልዶቫ ስህተት እንደሰራች እየተነገረ ነው። በአንድ ወር የጦርነት ሂደት የአሜሪካና ዩክሬን የህንድን ድጋፍ ያሳጣቸው ተብሎ ከተቀመጠው አንዱ የህንድ ተማሪዎች ጉዳይ ነበር። ተማሪዎቹ የአፍርካዊያንን ያህል ባይሆንም መውጫ አጥተው መቸገራቸው በበርካታ መገናኛ ብዙሃን ዘንድ መነጋገሪያ ሆኖ ነበር። ህንዳዊያኑን መንገድ ለመስጠት በሚል ሩሲያ የወሰደችው መፍትሄ በህንድ በኩል ምስጋና ተችሮታል ።በዚህም ህንድ ለነአሜሪካ ጥያቄ ዝምታን በማድረግ ለሩሲያ ያላት ውግንና በሰምና ወርቅ መልኩ ገልፃች። ወርቁ ገብቶናል ያሉት የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ጆ ባይደን “ህንድ ከአሁኑ ወዳጇ አሜሪካ ይልቅ የቀዝቃዛው ጦርነት አጋሯ እንደመረጠች አውቀናል ሲሉ ተደምጠዋል።

ጦርነቱ ከሶስት ሚሊየን በላይ ዜጎች ከቤታቸው እንዲፈናቀሉ አድርጓል። በጎረቤት ሀገራት በርከት ያሉ ዩክሬናዊያን የሞቀ አቀባበል ተደርጎላቸው የሚኖሩ ሲሆን ከኬብ ሳይወጡ በህንፃዎች ምድር ቤት የተጠለሉም ምድር ቤት ቁጥራቸው ቀላል አይደለም። በ30 ቀናት የስደተኞች ጉዞ በርካታ በረራ የተደረገባት ሀገር ስዊዘርላንድ መሆኗም ታውቋል።የ30 ቀናቱ የዩክሬንና ሩሲያን ጦርነት ለማርገብ በሚል ሁለት ሀገራት ቀዳሚ እርምጃ በተግባር አሳይተዋል። ቤላሩሲና ቱርክ።

ቤላሩስ በዝቅተኛ ዲፕሎማቶች መካከል የተደረጉ ውይይቶች ያስተናገደ ሲሆን ጦርነቱን ለማርገብ ሆነ ለማስቆም ግን አልሆነላትም። ቀጥሎም ቱርክ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴሮች ደረጃ ከፍተኛ የውይይት ድግስ አዘጋጅታ ብትጠራም የሚኒስትሮቹ መገናኘት ያመጣው ነገር አልነበረም ።የዩክሬን ፕሬዚዳንት ቮሎዶሚር ዘለንስኪ ከፕሬዚዳንት ቭላድር ፑቲን ጋር ፊት ለፊት መገናኘት አልፈልግም ያሉትም የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴቹ ውይይት ፍሬ አልባ መሆናቸው ተከትሎ ነበር።ዘለንስኪ የዘር ሀረጋቸው የሚመዘዝባት እስራኤልን በጦር መሳሪያ አልደገፍሽንም በሚል ቢወቅሱም የድርድርሩ ሁነኛ ቦታ ቴላቪቭ መሆኗን ግን ተናግረዋል። ጦርነቱ ካሳየን ገራሚ ነገር አንዱ አሜሪካና አውሮፓውያን ተረባርበው ስፖርትን ከፖለቲካው ጋር የቀላቀሉበት መንገድ ነው። ሩሲያን ከአለም ዋንጫ ፣ከአውሮፓ ሊጎችና ከማንኛውም የስፖርት ንግግር አግደዋታል። በዚህ ሳያበቃ የሩሲያ ባለ ሀብቶች ሲያስተዳድሩዋቸው የነበሩ ግለቦችም አደጋ ውስጥ እንዲወደቁ ተደርጓል።

አውሮፓዊያኑ እነዚህንና መሰል ጫናዎች በሩሲያ ላይ ቢያሳድሩም ዩክሬንን ኝ በምንም መልኩ የሚጠቅም አይደለም። ዩክሬን በእስካሁኑ ቆይታ ከ245 ቢሊየን በላይ ወይም ከ 75 በመቶ በላይ የሚሆኑ የሀገሪቱ የምጣኔ ሀብት እንቅስቃሴ ቆሟል። በሁለተኛ ደረጃ የተቀመጡ የምጣኔ ሀብት ስራዎች በግማሽ ያህል ጠፍተዋል። ሩሲያ በብዙ መንገድ ፈጥነው መጣል ያልቻሉት አካላት ፕሬዚዳንት ቮሎንድሚር ዘላንስኪ ኬቭን ለቀው እንዲወጡ ተጠይቀው ነበር። በሩሲያ ላይ ማዕቀብ የታልለችው ጃፓን ሳትቀር ፕሬዚዳንቱ ከሀገር እንዲወጡ ጠይቃለች። የሩሲያ ወዳጅ ናት የምትባለው ቻይና ጨምሮ የ18 ሀገራት መሪዎች ዘለንስኪ ኬቭን ላቀው በመውጣት የዩክሬንን ህዝብ ይታደጉ የሚል ጥያቄ አቅርበዋል።

ከሀገሬ የትም አልሄድም ብለው የፀኑት ዘላንስኪ የመላው ዓለም ድጋፍ ተማፅነዋል ።በመላው ዓለም ያሉ ሰዎች ሩሲያን የሚቃወም ሰልፍ እንዲያደርጉ ፕሬዚዳንቱ ጠይቀዋል። በአንድ አንድ ሀገራት ከፕሬዝዳንቱ ጥሪ በተቃራኒ “በሀገራችን ያሉ ሩሲያዊያን የጦርነቱ አካል አይደሉም”የሚሉ ሰልፎች ተካሂደዋል። የሩሲያ ባለስልጣናት ባለሀብቶች በውጭ ሀገራት ያስቀመጧቸው ሀብቶች አንዱ የወሩ መነጋገሪያ ነብር። የስዊዝ ባንክና አንድ አንድ ምዕራባዊያን ሀገራት ባንኮች 630 ቢሊዮን ዶላር ወይም 470 ቢሊየን ፓውንድ የሚበልጥ የሩሲያዊያንን ሀብት እንዳይቀንሳቀስ አግደዋል። በጦርነቱ የአንድ ወር ሂደት 5 ጋዜጠኞች ተጋድለዋል። ባውሊና ፣ሰርጌ ቶሚሊንኮ አሌክሲ ኮቫሌቭ ሜዱዛና አናስታሪያ ካሪሞቫ በጦርነቱ መሀል የተገደሉ የዩክሬንና ሩሲያ ዘጋቢዎች ናቸው።ሩሲያ በነዚህ ሁሉ ጫናዎች ውስት ብትሆንም የተበረከከች አትመስልም። ጦርነቱ እየገፋችበት ነው። አፀፋዊ የማዕቀብ ምላሾችንም እያጠናከረች መታለች ከበርካታ ሀገራት ጋር ባልት የንግድ ልውውጥ ዶላርን ከገበያ ውጪ አድርጋ በራሷ የመገበያያ ገንዘብ “ሩብል”ቀይራለች። በዩክሪን የተሰማሩ ወታደሮች በጀግንነት ግዳጃቸውን እንዲወጡ በሚል ልዩ መብቶች ሰጥታለች ። ከተባሉት ነገሮች ሁሉ ግን አሜሪካንን ባለስልጣናትን ያስበረገገው ሩሲያ አንዳች የሚያሰጋ ነገር አለ ቢዬ ከጠረጠርኩ የኒውክለር ጦር መሳሪያዬ ተግባር ላይ ይውላል ስትል ከባዱን ካርዷን በተጠንቀቅ አድርጋለች ። ጦርነቱ ግን ንብረት እያወደመ ፤አካል እያጎደለና የሰውን ህይወት እየቀጠፈ ቀጥሏል።Bloomberg,Anadolu,BBC, አልጀዚራ,Sky News The Gardian የዘገባው ምንጮች ናቸው።
በዘመድኩን ብሩ

Continue Reading

ሀገር ዉስጥ

የመቀንጨር አደጋ የተጋረጠበት በርካታ ማህበረሰብ በኢትዮጵያ በስፋት እንደሚገኝ ጥናቶች ያመላክታሉ።

Published

on

featured
Photo: Social Media

ኢትዮጵያ ካላት የህዝብ ቁጥር መካከል አብላጫውን ቁጥር የሚይዘው ማህበረሰብ በግብርና እንደሚተዳደር ይታወቃል።የሀገሪቱ ምጣኔ ሀብታዊ ፖሊሲም እስከቅርብ አመታት ድረስ ግብርና መር እንዲሆን ባለሙያዎች ሲናገሩ ይደመጣል። ይሁን እንጂ እስካሁን የምግብ ዋስትና ማረጋገጥ አለመቻሉን ለምን የሚያስብል ጉዳይ ነው። የምግብ ዋስትናን ካለማረጋገጥ ባለፈ በተለይ በገጠር የሚኖረውን ማህበረሰብ የተመጣጠነ ምግብ እጥረት እንዳለበት ይታወቃል።

በመሆኑም አሁንም ድረስ እንደሀገር የመቀንጨር አደጋ የተጋረጠበት በርካታ ማህበረሰብ በኢትዮጵያ በስፋት እንደሚገኝ ጥናቶች ያመላክታሉ። ይህ ደግሞ የትምህርት መዛባትን የጤናማ እና ብቁ ዜጋን ሊያሳጣ እንደሚችል ይገለፃል። የተጋረጠውን ሀገራዊ ችግር ለመቅረፍ የሚመለከታቸው ባለ ድርሻ አካላት ምን እየሰሩ ነው እንደ ሀገር የመቀንጨር አደጋ ምጣኔያችንስ ምን ያክል ደርሷል ስንል ባለሙያዎችን አነጋግረናል።

በኢትዮጵያ ከሁለት አመት በፊት በተደረገ ጥናት የመቀንጨር አደጋ 37 በመቶ የደረሰ ምጣኔ አለው። ይህ የመቀንጨር አደጋ በስፋት የሚታየው የ 6 ወር እስከ 59 ወር ያሉ ህፃናት ላይ ሲሆን እንደ ሀገር ከ6 ሚሊየን በላይ ከ5 አመት በታች ያሉ ህፃናት የመቀንጨር አደጋ አጋጥሟቸዋል ሲሉ በሰቆጣ ቃልኪዳን የፌዴራል ፕሮግራም ማስፈፀሚያ ዋና ሀላፊ ዶክተር ሲሳይ ሲናሞ ይናገራሉ። የመቀንጨር አደጋ እንደሀገር በጤና ላይ በትምህርት ላይ እና በሀገር ምጣኔ ሀብት ላይ ከፍተኛ ቀውስ ስለሚያስከትል ይህን ለመቅረፍ የሰቆጣ ቃልኪዳን ተቀርፆ እየተሰራ ነው ሲሉ ዶክተር ሲሳይ ሲናም ያክላሉ።

በሀገራችን የምግብና ስርዓተ ምግብ ችግር እንደሀገር ካሉ ቁልፍ ችግሮች መካከል አንደኛው እንደሆነ ጥናቶች ያሳያሉ። በሀገር ውስጥ የሚከሰቱ ተፈጥሮዋዊና ሰው ሰራሽ ችግሮች ደግሞ ይበልጥ ችግሩን ከፍ ሊያደርጉት እንደሚችሉ ይታወቃል። ይህን ችግር ለመፍታት ግን ዘለቂታዊነት ያለው የምግብና የአመጋገብ መመሪያና ፖሊሲ ተግባራዊ ማድረግ ያስፈልጋል ሲሉ የጤና ሚኒስቴር ዶክተር ሊያ ታደሰ ገልፀዋል። ምግብ አጠር በሆኑ አከባቢዎች ላይ እየተከሰተ የሚገኘው የመቀንጨር ችግር እንደሀገር በሰው ሀብት ልማት ላይ ተፅዕኖ ከመፍጠር ባለፍ በትምህርት ገበታ ላይ የሚገኙ ተማሪዎች የትምህርት ውጤታቸው አነስተኛ እንዲሆኑ እያደረገ ነው በማለት የትምህርት ሚኒስቴር ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ ተናግረዋል።

ትምህርት ሚኒስትርም የሚታየውን ችግር ለመቅረፍ የአመጋገብ ስርዓትን በመማርማስተማር ስርዓቱ ውስጥ ከመቅረፅ በተጨማሪ አዲስ በሚገነቡ ትምህርት ቤቶች ላይ የተመጣጥጠነ ምግብ ሊመረተባቸው የሚችሉ የእርሻ ቦታዎች በትምህርት ቤቶች እንዲዘጋጁ እየተደረገ ነው ሲሉ ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ ይጨምራሉ። በተመጣጠነ ምግብ እጥረት ምክኒያት የሚፈጠሩ ችግሮችን በዋነኝነት ለመፍታት የግብርናው ዘርፍ ሚናው ያልቀ በመሆ የግብርና ሚኒስቴርም የተመጣጠነ ምግብ እንደሀገር ተደራሽ ለማድረግ በቴክኖሎጊ የታገዘ ዘመናዊ የአመራረት ዘይቤን መከተል ስለሚያስፈልግ የተለያዩ ስትራቴጂካዊ አሰራሮች ተነድፈው ወደ ተግባር እየተገነባ ነው በማለት የግብርና ሚኒቴር ድኤታ ዶክተር ፍቅሩ ረጋሳ ገልፀዋል።

በምግብ እጥረት ምክኒያት የሚመጡ ሀገራዊ ችግሮች ከፍታቸው ከፍ ያለ በመሆኑ የመፍትሄ ሂደታቸው ከአንድ አቅጣጫ እንደማይመጣ ይታወቃል በመሆኑም ችግሩን ለመቅረፍ የተቀናጀ አሰራር ተግባራዊ ማድረግ ያስፈልጋል ተብሏል።
በዮሃንስ አበበ

Continue Reading

ሀገር ዉስጥ

በባለሙያ የታገዘ የፖሊሲ ማሻሻያ ማድረግ እና የተፍጥሮ ሀብት ላይ መሰረት አድርጎ መስራት አማራጭ የሌለዉ ነዉ።

Published

on

featured
Photo: bloomberg, women sitting in a market

በኢትዮጵያ የኑሮ ውድነት ከዛሬ ነገ መፍትሄ ይገኝለታል ተብሎ ቢጠበቅም ይበልጥ እየናረ እየናረ መቷል ። በእለት ከእለት ጠቀሜታ ላይ የሚውሉ የኢንዱስትሪ ምርቶች በአንዴ ከ 2 መቶ እስከ 4 መቶ ብር በላይ ጭማሪ ማሳየት መጀመራቸው ደግሞ ድንጋጤን እየፈጠረ ይገኛል ።
ችግሩን ደግሞ አስገራሚ የሚያደርገው የምርት ጥሬ እቃቸው ከሀገር ውስጥ ፍጆታ ባለፈ ለውጭ ገበያ በብዛት ማቅረብ የሚቻልባቸው ምርቶች መሆናቸው ተጠቃሚው ማህበረሰብ ለምን የሚል ጥያቄ የሚያስነሳ ሆኗል ።
ኢትዮጵያ በስፋት የምታመርታቸው የቅባት እህል ምርቶች የሀገር ውስጥ ፍጆታን የመሸፈን አቅም እንዳላቸው በተደጋጋሚ ሲነገር ቢደመጥም እንደ ዘይት እና መሰል ምርቶችግን ዋጋቸው ጣራ እየነካ ይገኛል።
እንደ ሀገር የውጭ ምንዛሬ በስፋት ከሚገኝባቸው ምርቶች መካከልም ይሄው የቅባት እህሎች መሆናቸው ለውጭ ፍጆታ የሚቀርቡት የሀገር ውስጥ ፍጆታን በቅድሚያ ሳይሸፍኑ ነው ወይ የሚሉ ጥያቄዎች እንዲነሳ ያደርጋል ።

አዋሽ ሬድዮም ለውጭ የሚላኩ ምርቶች ሳይቀንሱ በምን አይነት መንገድ ቢሰራ የሀገር ውስጥ ፍጆታን ማሟላት ይቻላል የሚታየውን ንረት ለማረጋጋት የሀገር ውስጥ ምርቶቻችን ላይ ምን ሊሰራ ይገባል ስንል የምጣኔ ሀብት ባለሙያዎችን አነጋግረናል ። በአለም አቀፍም ሆነ በሀገር ዉስጥ ያለዉ የንግድ ፖሊሲ የተስተካከለ አለመሆኑ ለኢንድስትሪ ግብአት የሚሆኑ ምርቶች በሀገር ዉስጥ እያሉን ምርቱን ኮዉጭ ለማስገባት እየተገደድን ስለሆነ ችግሮች በአለም አቀፍ ደረጃ ሲከሰቱ እኛም አብረን እንድንቸገር ተደርገናል ሲሉ የምጣኔ ሀብት ባለሙያዉ አቶ ያሬድ ሀይለመስቀል ይገልፃሉ ፡፡

አሁን ያለዉን የኑሮ ዉድነት ችግር ለመፍታት እና የሀገሪቱ ምጣኔ ሀብት እንዲስተካከል መንግስት የምጣኔ ሀብት ፖሊሲዉን እንደገና በባለሙያዎች ማስተካከያ ሊያደርግበት ይገባል ፡፡
በተጨማሪም ያለንን የተፈጥሮ ሀብት የምንጠቀምበትም መንገድ ሊመቻች ይገባል ሲሉ አቶ ያሬድ ይጨምራሉ ፡፡

በሀገር ዉስጥ በስፋት የምናመርተዉን የቅባት እህል እንኳን ሙሉ ለመሉ በሚባል ደረጃ ወደ ዉጭ በመላክ በምትኩ ለዘይት ማምረቻ የሚሆን ግብአት እያስገባን እንገኛለን ፡፡
ይህ በመሆኑ በዘይትም ሆነ በሌሎች መሰል ምርቶች ላይ የሀገር ዉስጥ አምራቾች ከገበያ እንዲወጡ በመደረጋቸዉ የዋጋም ንረት እና ሆነ የምጣኔ ሀብት ድቀት አድርሶብናል ያሉት ደግሞ ሌላኛዉ የምጣኔ ሀብት ባለሙያ ዶክተር ደምስ ጫን ያለዉ ናቸዉ ፡፡

በኢትዮጵያ አሁን ላይ እጅግ የጨመረዉ የዘይት ምርትን እንኳን ብናነሳ ከ ሁለት አስርት አመታት በፊት ተግባራዊ በተደረገዉ የፓልም ዘይት የቀረጥ ነፃ ማስገባት የግብይት አሰራር በዘርፋ ተሰማርተዉ የነበሩ አምራቾች ተወዳዳሪ እንዳይሆኑ አድርጓቸዋል ፡፡ በሌሎች ዘርፍም የሆነዉ ይህን መሰል አሰራር በመሆኑ ጥሬ ግብአት ወደ ዉጭ ልከን የተቀነባበረ እያስገባን በመሆኑ ላልተገባ ወጭ እየተዳረግን ነዉ ሲሉ የምጣኔ ሀብት ባለሙያዉ ዶክተር ቆስጠንጢኒዮስ በርኸ ተስፋ ይገልፃሉ ፡፡

ወደዉጭ ገበያ የምናቀርባቸዉ የሀገር ዉስጥ ምርቶች አብዛኛዎቹ ጥሬ ምርቶች በመሆናቸዉ ከምናገኘዉ ጥቅም ይልቅ የምናጣዉ ያመዝናል ፡፡ በመሆኑም ጥሬ የግብርና ምርቶችን ለዉጭ ገበያ ከማቅረብ ይልቅ የተቀነባበረ ምርት ማቅረብ ብንጀምር የምናገኘዉንም የዉጭ ምንዛሬ መጨመር እንችላለን በተጨማሪም ከዉጭ የምናስገባቸዉን የኢንዲስትሪ ግብአት እዚሁ በሀገራችን ማምረት የምንችልበት እድል ልናገኝ እንችላለን በማለት የምጣኔ ሀብት ባለሙያዉ አቶ ሳለ አምላክ ዘላለም ሀሳባቸዉን አንስተዋል ፡፡

እያናረ የሚገኘዉን የኑሮ ዉድነት እና እየወደቀ የሚገኘዉን የሀገርን ምጣኔ ሀብት እንዲያገግም ዋነኛ አማራጭ የሚሆነዉ ያለንን የተፈጥሮ ሀብት በተገቢዉ ሁኔታ መጠቀም ግዜ የማይሰጥ ጉዳይ ነዉ ሲሉ ዶክተር ቆስጠንጢኒዮስ ተናግረዋል ፡፡

የበርካታ ዜጎች እራስ ምታት የሆነዉን የኑሮ ዉድነት እና የምጣኔ ሀብት ድቀት ለማሻሻል በአፋጣንኝ በባለሙያ የታገዘ የፖሊሲ ማሻሻያ ማድረግ እና የተፍጥሮ ሀብት ላይ መሰረት ያደረጉ ስራዎችን መስራት አማራጭ የሌለዉ ጉዳይ እንደሆነ ባለሙያዎቹ ተናግረዋል ፡፡

በዮሃንስ አበበ

Continue Reading

በብዛት የተነበቡ