Connect with us

ሀገር ዉስጥ

በበጄት ዓመቱ ለ2.7 ሚሊዮን ዜጎች ቋሚ የሥራ ዕድል ተፈጥሯል :- የሥራና ክሕሎት ሚኒስቴር

Published

on

በበጄት ዓመቱ ለ2.7 ሚሊዮን ዜጎች ቋሚ የሥራ ዕድል ተፈጥሯል :- የሥራና ክሕሎት ሚኒስቴር

በበጄት ዓመቱ ለ2.7 ሚሊዮን ዜጎች ቋሚ የሥራ ዕድል መፈጠሩን የሥራና ክሕሎት ሚኒስቴር አስታውቋል።
ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ በየ ዓመቱ ለ2 ሚሊዮን ዜጎች ቋሚ የሥራ ዕድል እንዲፈጥር ተስቦ በ2014 ዓ.ም የተቋቋመ ዐዲስ ሚኒስቴር መሥሪያ ቤት ነው።

ሁለተኛው የሥራ ጉባዔ “ ዘላቂ ሥራ ለብሩህ ነገ ” በሚል መሪ ቃል ከነሐሴ 09 እሰከ 10 2014 ዓ.ም በሸራተን አዲስ ተካሒዷል።
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ሚኒስትር ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል ጉባዔውን በይፋ ሲክፈቱ እንደተናገሩት ሁለተኛው የሥራ ጉባዔ በሥራ ዕድል ፈጠራ ፣ በቴክኒክና ሙያ ዘርፍ እና የሥራ ደህንነት ዘርፎች ጠቃሚ የሆኑ የፖሊሲ ግብአቶች የሚገኝበት ነው፡፡

በሃገራችን ከፍተኛ የሆነ ሥራ አጥነት መኖሩ፣ የፈጠራና ክሕሎት ልማዶች አነስተኛ መሆናቸው እና በኢንዱስትሪው ዘርፍ ሠፊ ንቅናቄ መፍጠር ማስፈለጉ ደግሞ ለመሥሪያ ቤቱ በሚኒስቴር ደረጃ መቋቋም ሌላ ገፊ ምክኒያት ነው።

የሥራና ክሕሎት ሚንስትር ወ/ሮ ሙፈሪያት ካሚል በሃገራችን ሠፋፊ የሥራ ዕድሎችን ካልፈጠርን የሥራ አጡ በቁጥር በየ አመቱ ባያሌው የሚጨምር መሆንኑ አውቀናል ብለዋል። ስለሆነም ከታቀደው በላይ መሥራት ያሻልም ብለዋል።

በበጀት ዓመቱ በርከት ያሉ ጊዜአዊ የሥራ ዕድሎች ተፈጥረዋል ያሉት ሚኒስቴሯ በቋሚነት ለ2.7 ሚሊዮን ዜጎች ሥራ መስጠት ተችሏል ባይ ናቸው። ስኬቱ የሚያኩራራና አይደለም ፤ ከዚህ በላይ መሥራት ግድ ይለናል የሚለውንም ጨምረዋል።

የሥራ ዕድል ፈጠራውን የግብርናው መሥክ በስፋት እንዲሸፍን የመንግስት ፖሊሲ ነው ያሉት ወ/ሮ ሙፈሪያት ካሚል በዚህም መሠሰት 46 በመቶውን እንዲሸፍን ታስቧል ብለዋል። ነገር ግን በዓመቱ 26 በመቶውን ብቻ እንደሸፈነ ጠቅሰው ለዚህ አነስተኛ ስኬት መገኜት ማነቆ የሆኑት የኢንዱስትሪ ትስስር አለመኖር እና የግብርና ምርቶች ላይ እሴት ጨምሮ መሸጥን አለመለማመዳችን ነው ሲሉ አስረድተዋል።

ሥራ ሁለንተናዊ ዕይታ እና ምልከታ ይፈልጋል ያሉት ሚኒስቴሯ ሙፈሪሃት ተበታትነው የነበሩ ሥራን ማዕከል ያደረጉ ተቋማትን ወደ አንድ በመሰብሰብ ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ከተቋቋመ በኋላ ዘርፎቹ ያሉባቸውን ማነቆዎች ለመፍታት ጥረት እየተደረገ ይገኛልም ብለዋል፡፡

የሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ምሰሶዎች በሆኑት የሥልጠና፣ የሥራ ዕድል ፈጠራ እና የኢንዱስትሪ ሰላም ወይም የሥራ ቦታ ደህንነት ዘርፎች የገበያውን ፍላጎት መሰረት ያደረጉ ሰፊ ሥራዎች ሲሰሩ መቆየታቸውን በመግለፅ ከተለያዩ አጋር አካላት እና ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች ጋር የተፈጠሩትን የቅንጅት ሥራዎች ከጅምር እንቅስቃሴዎች መካከል ሚኒስትር ሙፈሪሃት በቀዳሚነት ጠቀሰዋቸዋል፡፡

በሰሜኑ የሃገራችን ክፍል በነበረው ጦርነትና በሌሎችም አካባቢዎች ያሉ የማያቋርጡ ግጭትና ውድመቶች በሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ እንቅስቃሴ ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ መፍጠሩንም ተናግረዋል።

ተቋምን እያቋቋመ በጦርነት የወደሙ ኢንተርፕራይዞችን እና ቴክኒክና ሙያ ተቋማትን በመደገፍ ባለፉት ወራት ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ በርካታ ሥራዎችን ማከናወኑን የተናገሩት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ሁለተኛው የሥራ ጉባዔ በማይቋረጠው የለውጥ ሂደት ውስጥ ለሚተገበሩ ዘርፈ ብዙ ሥራዎች የፖሊሲ ሃሳቦችን አንጥሮ እንደሚያወጣ እንጠብቃለን ብለዋል ፡፡

ሁለተኛው የሥራ ጉባዔ ዘርፉን የተመለከቱ ፖሊሲዎች፣ ስትራቴጂዎች፣ ደምቦችና መመሪያዎች እንዲሁም አሰራሮችን ለመፈተሽ የሚያግዙ ሀሳቦች የሚሰባሰቡበት እና የዘርፉ ባለሙያዎች የሚበረታቱበት ነው ያሉት ደግሞ
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የሥራ፣ ሥራ ስምሪትና ገበያ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታው አቶ ንጉሡ ጥላሁን ናቸው።

የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ያዘጋጀው የሥራ ጉባዔ ተሳታፊዎች ልምድ የሚለዋወጡበት ፣ ከሚቀርቡ ችግር ፈቺ ጥናቶች የፖሊሲ ግብአቶች የሚገኝበት፣ የዲጂታሉን ዓለም ለሥራ እና ስልጠና ለመጠቀም የሚያስችል ውይይት የሚካሄድበት መሆኑንም አቶ ንጉሡ ተናግረዋል፡፡

ከስልጠና እና ከፋይናንስ አኳያ በተሻለ ሁኔታ ኢንተርፕራይዞችን የደገፉ የቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች እና አነስተኛ የፋይናንስ ተቋማት ዕውቅና የሚያገኙበት ሁለተኛው የሥራ ጉባዔ ውጤታማ ሥራ ፈጣሪ ወጣቶችን መነሻ በማድረግ ንቁ እና ለሥራ የተዘጋጀ ወጣት በመፍጠር ሂደት በተለይም ለሚያጋጥሙ ችግሮች መፍትሔ የማበጀት ዘርፈ ብዙ ጥቅሞች እንደሚኖሩት ተስፋ አለኝም ብለዋል፡፡

ለጉባዔው ከቀረቡ 15 ጥናታዊ ፅሁፎች መካከል በባለሙያ የተመረጡት 4ቱ ቀርበው ውይይት የሚደረግባቸው ሲሆን በሠራተኛ አቅርቦት፣ ፍላጎት እና በሥራ ሥምሪት ትስስር፣አፈፃፀም፣ ተግዳሮች እና መፍትሄዎች ላይ የሚመክር ፓናል ውይይትም ተካሒዷል፡፡

በዲጅታል የሥራ ፈጠራ ዘርፍ በተሰማሩ አካላት መካከል በሀገሪቱ የዲጂታል ኢንተርፕርነርሽፕ ሥነ-ምህዳር ግንባታ ረገድ የመንግስትና የግሉን ዘርፍ ሚና እና ድርሻ እንዲሁም መልካም አጋጣሚዎች፣ ተግዳሮቶች መፍትሄዎቻቸው ላይ በዘርፉ ምሁራን እና ባለሙያዎች የሚደረገው ውይይትም የጉባዔው አካል መሆኑን አቶ ንጉሡ ገልፀዋል፡፡

ከተለዩት 10 የንግድ ሥራ ሃሳብ ባለቤቶች በዚህ ጉባዔ 5 ዳኞች በተገኙበት የንግድ ሥራ ሃሳባቸው ቀርቦ ከ10ሩ ውስጥ ምርጥ 3 ተለይተው ለንግድ ሥራቸው መጀመሪያ የሚሆን የገንዘብ ሽልማት ይበረከትላቸዋል፡፡

የተሻለ አፈፃፀም ያስመዘገቡ 60 የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ ጣቢያዎች እንዲሁም 60 ባለሙያዎች፣ 280 ወደ ታዳጊ የተሸጋገሩ ኢንተርፕራይዞች፣ 102 የላቁ ሞዴል ኢንተርፕራይዞች፣ 6 ለኢንተርፕራይዞች ድጋፍ ያደረጉ የቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች እና ተቋማት፣ 3 ለኢንተርፕራይዞች ድጋፍ ያደረጉ የአነስተኛ ፋይናንስ ተቋማት ፣ 3 የተሻለ አፈፃፀም ያላቸው የግብርና ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ተቋማት ዕውቅና እና ሽልማት ተሰጥቷቸዋል፡፡

በሃገራችን በየ ዓመቱ ለመፍጠር የታለመው ዐዲስ የሥራ ዕድል ግቡን እንዲመታ ከሁሉም የመንግስትና የግሉ ተቋማትና ድርጅቶች ብዙ እንደሚጠበቅም ሚንስትሯ ወ/ሮ ሙፈሪያት ከሚል ተናግረዋል።

በ ያለው አዛናው

 

 

ሀገር ዉስጥ

የከንፈር እና የላንቃ መሰንጠቅ ህጻናት ከመወለዳቸው በፌት የሚከሰት ችግር ሲሆን በእርግዝና ወቅት የህጻኑ/የህጻኗ ከንፈር ወይም ላንቃ ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል ሳይገጥም ሲቀር የሚፈጠር ክፍተት /ስንጥቅ ማለት እንደሆነ የህክምና ባለሙያዎች ያስረዳሉ ።

Published

on

የከንፈር እና የላንቃ መሰንጠቅ ህጻናት ከመወለዳቸው በፌት የሚከሰት ችግር ሲሆን በእርግዝና ወቅት የህጻኑ/የህጻኗ ከንፈር ወይም ላንቃ ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል ሳይገጥም ሲቀር የሚፈጠር ክፍተት /ስንጥቅ ማለት እንደሆነ የህክምና ባለሙያዎች ያስረዳሉ ። በአለማችን ላይ በየአመቱ ከ170.000 በላይ ህጻናት ከከንፈር እና ከላንቃ መሰንጠቅ ጋር ይወለዳሉ ። በአፍሪካ ውስጥም ከ32.000 ህጻናት በላይ በየአመቱ ከዚሁ ችግር ጋር ይወለዳሉ ። እንዲሁም ደግሞ በሃገራችን ኢትዮጵያ በየአመቱ ከ3000 በላይ ህጻናት ከከንፈር እና ላንቃ መሰንጠቅ ጋር ይወለዳሉም ተበሏል። ይህም ህጻናቱ ለአመጋገብ ፣ለአተነፋፈስ እንዲሁም ለአነጋገር እክሎች ያጋልጣቸዋል ነው የተባለው ። ስማየል ትሬን በአለማችን የከንፈር እና የላንቃ መሰንጠቅ ጋር ለተወለዱ ህጻናት የማስተካከያ ቀዶ ጥገና በነፃ የሚሰጥ በጎ አድራጎት ድርጅት ነው ። ስማይል ትሬን ከሰን ኢኮ አርት ፎር ሶሻል ደቨሎፕመንት ጋር በመተባበር “ሙቪንግ ስማይል” የተሰኘ የአስፋልት ላይ ባቡር መሰል መኪና በማዘጋጀት፤ አገር አቀፍ የከንፈር እና ላንቃ መሰንጠቅ የግንዛቤ ማስጨበጫ ጉዞ በይፉ መጀመሩን የሰን ኢኮ አርት ፎር ሶሻል ደቨሎፕመንት ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኤፍሬም በቀለ ተናግረዋል። ከ1999 ጀምሮ በአለማችን ላይ የክንፈር እና የላንቃ መሰንጠቅ ላጋጠማቸው 1.5 ሚሊየን ህጻናት ቀዶ ጥገና በነጻ አድረገዋል ተብሏል ። በኢትዮጵያም ከ 2007 ዓ.ም ጀምሮ ከ32.000 ህጻናት እና ወጣቶች በላይ የነጻ ቀዶ ጥገና ህክምና እና አገልግሎት እየተሰጠ ይገኛልም ነው የተባለው ። ስማይል ትሬን በኢትዮጵያ ከ2007 ጀምሮ ከ32 ሺሕ ህጻናት እና ወጣቶች በላይ የነፃ ቀዶ ጥገና ህክምና እና አገልግሎት መስጠቱን የገለጹት በምስራቅ አፍሪካ የስማይል ትሬን ረዳት ፕሮግራም አስተባባሪ ዶ/ር ቤተል ሙሉጌታ ሲሆኑ፤ ከዚህም በተጨማሪም ድርጅቱ ከከንፈር እና ላንቃ ጋር ተያይዞ ነጻ የጥርስ ህክምና፣ የአመጋገብ ምክር፣ የንግግር ህክምና (speech therapy)፣ የማህበራዊ እና ስነ ልቦናዊ ድጋፍ እና ሌሎችም አገልግሎቶችን የያዘ ኹሉን አቀፍ የአገልግሎቶችን በመስጠት ላይ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ዶ/ር ቤተል አክለውም ስማይል ትሬን በአገር ውስጥ ለሚገኙ የግል እና የመንግስት ሆስፒታሎች እና ሀኪሞች የቀዶ ጥገና ህክምና ስልጠናዎችን በመስጠት ዘላቂ የሆነ መፍትሄዎችን እዚሁ ባሉ የጤና ባለሙያዎች እንዲሰጥ እያደረገ እንደሚገኝም አስረድተዋል። የከንፈር እና የላንቃ መሰንጠቅ ጋር ተያይዞ ችግር ያለባቸው የማህበረሰብ ክፍሎችም፤ ድርጅቱ የነጻ ጥሪ ማዕከል 9889 ላይ በነጻ በመደወል ለህክምናው መመዝገብ፣ መረጃ ማግኘት እና መማር እንደሚችሉ ተገልጿል።
በመቅደላዊት ይግዛው

Continue Reading

ሀገር ዉስጥ

በአዲስ አበባ በክርና ፕላስቲክ ፋብሪካ ላይ በደረሰ የእሳት አደጋ 8 ሚሊየን ብር የሚገመት ንብረት ማዳን እንደተቻለ 2 ሚሊዮን ብር የተገመተ ንብረት መውደሙ ተገለፀ ።

Published

on

በአዲስ አበባ በክርና ፕላስቲክ ፋብሪካ ላይ በደረሰ የእሳት አደጋ 8 ሚሊየን ብር የሚገመት ንብረት ማዳን እንደተቻለ 2 ሚሊዮን ብር የተገመተ ንብረት መውደሙ ተገለፀ ።

በአዲስ አበባ ከተማ ሰኞ ምሽት 1ሰዓት ገደማ በአቃቂ ክፍለ ከተማ ወረዳ 7 ልዩ ቦታዉ ቃሊቲ ኢንደስትሪ መንደር ውስጥ በክርና ፕላስቲክ ፋብሪካ ላይ በደረሰ የእሳት አደጋ 2 ሚሊዮን ብር የተገመተ ንብረት መውደሙን የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አስታውቃል። የደረሰዉን የእሳት አደጋ ለመቆጣጠር ሶስት የአደጋ መቆጣጠር ተሽከርካሪ ሃያ አንድ የአደጋ ጊዜ ሰራተኞች መሰማራታቸውን የኮሚሽኑ የህዝብ ግንኙነት ባለሙያ አቶ ንጋቱ ማሞ ለአዋሽ ሬዲዮ ተናግረዋል።

አደጋውን ለመቆጣጠር ሁለት ሰዓት መፍጀቱን አስታውቀዋል። የእሳት አደጋዉ ተስፋፍቶ አደጋዉ በደረሰበት ፋብሪካ ከዚህ የበለጠ ጉዳት እንዳይደርስና በአካባቢዉ ባሉ ፋብሪካዎች እንዳይዛመት ማድረግ ተችሏል ያሉ ሲሆን ። የአደጋ ጊዜ ሰራተኞቹ ባደረጉት ርብርብም 8 ሚሊየን ብር የሚገመት ንብረት ማዳን እንደተቻለ እና አደጋዉ በሰዉ ላይ ምንም ጉዳት አልደረሰም። የአደጋው የመነሻ ምክንያት በመጣራት ላይ ይገኛል በለዋል ።

በመጨረሻም ባሳለፈነው ቅዳሜና አሁድ በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ 1 እና ወረዳ 12 ክፍቱን በተተወ ዉሀ በአቆረ ጉድጓድ ዉስጥ እድሜያቸዉ 12 እና 25 የሆኑ ታዳጊና ወጣት ህይወታቸዉ ማለፉ ተገልጿል ። በአቃቂ ወረዳ 1 እድሜዉ 25 ዓመት የሆነ ወጣት ወንዝ ዉስጥ ገብቶ ህይወቱ አልፎ ተገኝቷል።

የአደጋ ጊዜ ሰራተኞች አስከሬኑን አዉጥተዉ ለፖሊሰ አስረክበዋል ነው የተባለው ። ሌላኛዉ አደጋ እለተ እሁድ 10 ሰዓት ገደማ በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለከተማ ወረዳ 12 ታዳጊዎች ተቆፍሮ ክፍቱን የተተወና ዉሀ ባቆረ ጉድጓድ ዉስጥ ዋና ለመዋኘት ከሄዱ ሶስት ታዳጊ ተማሪዎች መካከል እድሜዉ 12 ዓመት የሆነው የስድስተኛ ክፍል ተማሪ ታዳጊ ዋና ለመዋኘት ገብቶ ህይወቱ አልፎ ተገኝቷል።

የዚህ ታዳጊ አስከሬን በፍለጋ የተገኘዉ ሰኞ ማለዳ ነዉ። አስከሬኑንም ፖሊስ ተረክቧል። በአዲስ አበባ የሚገኙ ወንዞችና በተለይም ክፍቱን የተተዉ ዉሀ ያቆሩ ጉድጓዶች እየተበራከቱ በመምጣታቸዉ ወላጆች ታዳጊ ልጆቻቸዉ እንዲሁም ወጣቶች በወንዞችና ዉሀ ያቆሩ ጉድጓዶች አካባቢ የሚኖራቸዉን እንቅስቃሴ እንዲያቆሙ ማድረግ ያስፈልጋል። በ2014 ዓ.ም ክፍቱን በተተዉና ወሀ ባቆሩ ጉድጓዶች ዉስጥ እድሜያቸዉ 7 እና 15 የሚገመት ታዳጊዎች በእነዚህ ወሀ ባቆሩ ጉድጓዶች ዉስጥ ገብተዉ ህይወታቸዉን ማጣታቸው የሚታወስ ነው ።

በያዝነዉ በ2015 ዓ.ምም መስከረምና ጥቅምት ወር 3 ታዳጊዎች ህይወታቸዉን አጥተዋል። ችግሩ ረጅም አመታትን ያስቆጠረና እየቀጠለ የመጣ ችግር በመሆኑ ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ እሙን ነው ። እንዲህ ባለዉ አደጋም በየአመቱ በአማካይ 12 ታዳጊዎች ህይወታቸዉን ያጣሉም ተብሏል ።

በመቅደላዊት ይግዛው

Continue Reading

ሀገር ዉስጥ

ኢትዮጵያ ለአለም ገበያ ከምታቀርበው የቡና ምርት ዉስጥ 55 በመቶ የሚሆነዉ ከደረጃ በታች መሆኑ ተገለፀ።

Published

on

ኢትዮጵያ ለአለም ገበያ ከምታቀርበው የቡና ምርት ዉስጥ 55 በመቶ የሚሆነዉ ከደረጃ በታች መሆኑ ተገለፀ።
ለኢትዮጵያ ምጣኔ ሀብት የጀርባ አጥነት ሆኖ እያገለገለ ያለዉ የቡና ምርት ለሀገሪቱ ከፍተኛ የዉጭ ምንዛሬ ከማስከገኘቱ በተጨማሪ ሩብ ለሚሆነዉ የኢትዮጵያ ህዝብ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ መተዳደሪያ እንደሆነ መረጃዎች ያመላክታሉ።
ከስድት ሺህ በላይ የቡና ዝርያ እንዳላት የሚነገርላት ኢትዮጵያ እስካሁን እየተጠቀመችዉ ያለዉ የቡና ዝርያ በጣት የሚቆጠር ብቻ ነዉ ተብሏል ።
ሀገሪቱ ለቆላዉም ለደጋዉም ለወይናደጋዉም ለሶስቱም አይነት የአየር ንብረት ተሰማሚ የሆነ የቡና ዝርያ ቢኖራትም ከዘርፉ ማግኘት የሚገባትን ጥቅም በተለያዩ ምክንያቶች እያገኘች እንደልሆነ የኢትዮጵያ ቡና እና ሻይ በለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ዶክተር አዱኛ ደበላ አንስተዋል።
ለዚህም ማሳይ ደግሞ በዝንድሮው አማት ከተለያዩ አለም ሀገራት ለአለም ገበያ ከቀረበዉ 174 ሚሊዮን በላይ ኬሻ ቡና ኢትዮጵያ ማቀረብ የቻለችዉ 5 ሚሊዮን ብቻ ነዉ ያሉት ዳይሬክተሩ ይህም ካለን የቡና ሀብት እና ተስማሚ የአየር ንብረት አንጻር ሲታይ በእጅጉ የወረደ ነዉ ብለዋል።
ይህም ሀገሪቱ ያላትን ሀብት በአግባቡ አለመጠቀሟ በምጣኔ ሃብቷ ላይ እና በዘርፉ ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ ማሳደሩን ተነግሯል።
ኢትዮጵያ በያመቱ ለአለም ገበያ የምታቀርበዉ ቡና መጠኑ እየጨመረ ቢመጣም ከዉጪ ንግዱ የምናገኘዉ የገቢ መጠን ግን በእጅጉ ወርዷል ብለዋል፡፡
የአለም የቡና ገበያ እና የኢትዮጵያ ቡና ገበያ በምንያክል መልኩ ነዉ እየሄደ ያለዉ ስንል ላደረግነዉ ጥናት የኢትዮጵያ ቡና ተስፋ ሰጪ አይደለም የሚል ግኝት ላይ መድረሳቸዉን ዳይሬክተሩ ተናግራዋል ፡፡
ለዚህም ምክኒያት ደግሞ ኢትዮጵያ በብዛት የምታመርተዉ ቡና ደረጃ አምስት ወይም ሂዉጅ የሚባሉ ቡናዎች በጨረታ እና በኒዎርክ ገበያዎች ላይ የሚሸጡ መሆናቸዉን ተናግረዋል ፡፡
እነዚህ ቡናዎች ደረጃቸዉም እጅግ የወረደ በጫራታ የማይሸጡ ተደራድረን እንኳን ለመሸጥ የማይሆኑ ናቸዉ ሲሉም አከለዋል ፡፡ እነዚህ ቡናዎች በአለም ገብያ ከሚቀርቡ የኢትዮጵያ ቡናዎች 55 በመቶዉ ድርሻ የሚዙ እንደሆኑም ተነግሯል፡፡
ኢትዮጵያ በአለም ገበያ በሰፔሻለለቲ ደረጃ የምትሸጠዉ 15 በመቶ ብቻ ነዉ፡፡ ይህን ችግር ቀርፈን የቡናዎቻችንን ደረጃዎች ማሻሻል ካልቻልን በሚጠበቀዉ ልክ ከዘርፉ የሚገኘዉን የዉጭ ምንዛሬ ማሳደግ ያዳግታል ብላዋል።
የኢትዮጵያ ቡና አሁን ላይ በሶስት የተለያዩ የሰዉ ሰራሽ እና የተፈጥሮ ችግሮች እንደተደቀኑበትም ባለስጣኑ አመላክቷል ፡፡
በዚህም አንደኛ የአለም የቡና ዋጋ መዋዠቅ ሲሆን ይህም አረሶ አደሩ የቡና ዋጋ በቀነሰ ቁጥር ከቡና ምርት ወደ ሌላ ምርቶች ለመግባት ይገደዳል፡፡
በሁለተኛ ደረጃ የአየር ንብረት ለዉጥን እንደችግር ያነሱት ዳይሬክተሩ ኢትዮጵያ በብዛት የምታመርተዉ የአረቢካ ቡና ስለሆነ ይህም የቡና ዝርያ በሙቀት ሰለሚጠቃ የአለም ሙቀት በአንድ ዲግሪ በጨመረ ቁጥር የቡና ምርት ተፈላጊነት በእጅጉ እንደሚቀንስ አመላክተዋል፡፡
በሶስተኛ ደረጃ ደግሞ የሃገሪቱ የደንን መመናመን ለዘርፉ ከፍተኛ ስጋቶች መሆናቸዉ በተግዳሮትነት ተወስቷል፡፡
ያሬድ እንዳሻዉ

Continue Reading

በብዛት የተነበቡ