Connect with us

ቴክኖሎጂ

ራድዮ በኢትዮጰያ ታሪካዊ ዳራ እና ያበረከተዉ አስተዋጽኦ

Published

on

featured
Photo: FarmRadio

ራድዮ በኢትዬጰያ ታሪካዊ ዳራ 

ራድዮ እና ኢትዬጵያ የተለየ ቁርኝት እንዳላቸው ብዙ ማሳያዎች እንዳላቸው ማንሳት እንችላለን፡፡ ራድዮ በኢትዮጵያ የተጀመረው በቀዳማዊ ኃ/ሥላሴ ዘመነ መንግስት ሲሆን ጊዜውም 1931 ዓ/ም አካባቢ እንደነበር መረጃዎች ይገልጻሉ፡፡ የራድዮ አጀማመር በኢትዬጵያ ከአፍሪካ ቀደምት እና ፈርቀዳጅ መሆኑ ይታወቃል፡፡

በዘመኑ በዚህ የራድዮ ሞገድ የሚተላለፉ ፕሮግራሞች ኢትዮጵያዊያን በናፍቆት የሚጠቡቋቸውና በጉጉት የሚያደምጡአቸው የመገናኛ ብዙሃን አንዱ እና ዋንኛው ነበር፡፡ ይሄም ራድዮ አንድ ለእናቱ ነበር እና በርካታ አስተዋፅኦ አድርጓል፡፡ አሁን ላለንበት የመገናኛ ብዙሃን በተለይ የራድዮ ሞገድ ቀድሞ የነበረው የራድዮ መቋቋም ትልቅ አስተዋጽኦ አበርክቷል፡፡

ይህ የኢትዮጵያ ራድዮ ተብሎ የሚጠራው የመጀመሪያው ቀደምት የመገናኛ ብዙሃን አሁን ላሉት የሬድዮ ሞገዶች መንገድ በመጥረግ ረገድ ትልቅ አበርክቶ ነው፡፡ ለዚህ የራድዮ ሞገዶች መቃናት በርካቷች አስተዋጾ አድርገዋል፡፡ በርካታዎችም ዋጋ ከፍለዋል፡፡ ቀደምትም የኢትዬጵያ ራድዮ የተለያዩ ፈተናዎችንና ተግዳሮችን አልፎ ሲመጣ በርከት ያሉ የራድዮ ሙያተኞች እንዲሁም ጋዜጠኞች ትንሽ የማይባል ዋጋ ከፍለዋል፡፡

በዚያን ጊዜ….አሁን መረጃ እንደልብ እደሚዛቅበት ወቅት ሳይሆን በጊዜው መረጃ ለመፈልፈል ሙያተኞቹ የማይፈነቅሉት ድንጋይ የማያንኳኳት በር እንደሌለ አያሌ መዛግብቶች ምስክር ናቸው፡፡ በኢትዮጵያ የራድዮ ፍቅር የተለየ ነው፡፡ ምክንያቱም በዘመኑም ይሁን አስካሁን ቅርብ ጊዜ ድረስ ኢትዮጵያውያን ራድዮ ለመስማት አቴና ሰቅለው ከግርግዳ አንጠልጥለው የሚያዳምጡበት ጊዜ እሩቅ አልነበርም፡፡

እንዲሁም ራድዮ ለመስማት በአንድ ቤት ውስጥ መሰብሰብ ካማይረሱ ትውስታዎች መካከል ነበር፡፡ ራድዮ ለመስማትም ሩቅ ቦታ መሄድ የተለመደ ነበር፡፡ ዜናዎችን ለመስማት ካንዱ መንደር ወደሌላኛው መንደር ሄደው መስማት ከማይረሱ ትዝታዎች መካከልም ነበር፡፡ ራድዮ አሁንም በኢትዮጵያ ውስጥ በሚሊዮኖች የሚደመጥ ከመገናኛ ብዙሃን ዘርፍ አንዱ ነው፡፡ በዘመኑ ኢትዮጵያውያን ሁሉንም መረጃዎች የሚያገኙበት ብቸኛ አማራጭ የኢትዮጵያ ራድዮ ነበር፡፡

አሁን በርግጥ እንዲህ በአጫጭር ሞገዶች ኤፍኤሞች የተበራከቱበት ጊዜ ቢሆንም እንደ ራድዮ አጀማመሩ ለውጡ ዘገምተኛ መሆኑ ይነገርለታል፡፡ ይህ መገናኛ ብዙሃን ዘርፉ እንደቀደምትነቱ የበለጠ መሻሻል ፣ ማደግ ይኖርበታል፡፡ እንዲሁም እራሱን ችሎ በመቆም ትልቅ ተቋም መሆኑን ማስመስከር እና በተግባር መገለጽ ይጠበቅበታል፡፡

ራድዮ በኢትዮጵያ በዘመናት ያበረከተው አስተዋፅኦ
ራድዮ በኢትዮጵያ በነበረው አስተዋፆ እንዲህ በቀላሉ የሚለካ አልነበረም ምክንያቱም ኢትዮጵያውያን በፍቅር ይሰሙታል ያደምጡታል ፡፡በዚህ መካከል የባህል መወራረስ፣የአንዱን ባህል ለሌሎች ለማስተዋወቅ እና አንዱን ማህበረሰብ ከሌላኛው ማህበረሰብ ጋር ለማቀራረብ ለማስተዋወቅ ትልቅ አስተዋጽኦ ነበረው፡፡

አብሮነት ከማጉላት አንፃር አንድነት ከማፅናት አንጻር እንደ ትልቅ ድልድይ ስንጠቀምበት የነበረው የራድዮ ሞገድ ነው፡፡የራድዮ የመገናኛ ብዙሃን በርካቶች የሚያደምጡት፣ መረጃ የሚያገኙበት፣ እውቀት የሚሸምቱበት እንዲሁም አሳባቸውን የሚገልጹበት እና የሚወያዩበት የመገናኛ ዘርፍ ነበር።

በተለይም እውነተኛ መረጃ ለህዝብ ከማቅረብ አንጻር እንዲሁም በህብረተሰቡ እና በመንግስት መካከል መተማመን እንዲኖር የዚህ የመገናኛ ብዙሃን አስተዋፅኦ የላቀ እንደነበር ማወቅ ይቻላል፡፡ እንዲሁም መረጃን በቶሎ ለማህበረሰብ ከመስጠትና ከማቀበል ጎን ለጎን በህብረተሰቡ መካከል ያሉ ወግ፣ልማድ፣ማንነት እንዲሁም ባህልን ከማሳደግ አንጻር ከፍተኛ ሚና ነበር፡፡

በተጨማሪም የአንዱን ማህበረሰብ ወግና ልማድ ስርአትና እሳቤ ለሌሎች ለማጋራት የራድዮ አስተዋጽኦ እንዲህ በቀላሉ የሚዘነጋ አይደለም። ለአንድ ሀገር እድገትና ብልጽግና የሀገር ሰላምና አንድነት ቀዳሚ ጉዳይ ይሆናል የራድዮ መገናኛ ብዙሃን ሰላምን ከማስፈንና ከማስጠበቅ አንጻር ከፍተኛ ድርሻ ይኖራቸዋል፡፡

በየጊዜያቱ እነዚህን የሰላም ጉዳዮች ከማህበረሰቡ ጋር በመመካከር እና አሳብ በመስጠት የተለያዩ የሰላም ጉዳዬችን በመቅረጽ እና በማስተጋባት ለህዝብ እዲደርስ መደረጉ የበለጠ ራድዮ ለሰላም ያለውን ዋጋ አሳድጎቷል፡፡

ራድዮ በኢትዮጵያ ውስጥ ሰላማዊ የፖለቲካ ሽግግር እንዲሁም የሀሳብ መቀራረብ እንዲኖር አበርክሮቶ የላቀ ነበር፡፡ መቻቻል እና አብሮ መኖር እዲጠነክር፣ወደጅነት እዲበረታ፣ሰዎች ሀሳባቸውን በነጻነት እንዲገልጹ ሚድያው የራሱን ድርሻ ተወጥቶል፡፡

የሀሳብ ነጻነት በቀላሉ እዲሸራሸር ሁሉም ያለውን ሀሳብ ለህዝብ እዲያደርስ እንዲሁም የተለያዩ ሀሳቦች ለብዙሃኑ ከማቅረብ አንጻር ከፍተኛ አስተዋጽኦ ነበረው በየዘመናቱ የሚነሱ የፖሊታካ ትኩሳቶችን በማብረድ እና አሳቦች ተቀራርበው ፍሬ አፍርተው ለሀገር ጥቅም እንዲሁሉ የራሱን ድርሻ ተወቷል፡፡
ሀገር እንደ ሀገር እድትቀጥል እውነተኛ እና ታማኝነት ያላቸው መረጃዎች ለማህበረሰቡ ለማድረስ ራድዮ በርካታ መንገዶችን ተጉዘዋል፡፡

ቤንኦን ጌታቸዉ

Click to comment

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ማህበራዊ

ያልተሠራበት የጤና ገበያ – በትዉልደ ኢትዮጵያዉያን እና በኢትዮጵያ

Published

on

featured
Photo: Hakim Consult

የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በየአመቱ ላለፉት 13 ዓመታት በ 10.8 በመቶ እያደገ እና በአከባቢዉ ካሉት ከፍተኛ እደገት ከሚያሳዩ ሀገራት ተርታ ላይ አስቀምጧታል። የሀገሪቱም የአፍሪካ ቀንድ አቀማመጥ እና የአፍሪካ ህብረት መቀመጫ መሆኗ ለተለያዩ የመካከለኛዉ ምስራቅ እና ሌሎችም የገበያ እድሎች ለዚህ እድገት ቀጣይነት ምክንያት ሊሆኑ ይችላሉ።
ከዚህ ቀደም የነበሩቱ አብዛኛዎቹ የኢኮኖሚ እድገቶች በግብርና፣ ገጠር ልማት፣ መሰረተ ልማቶች እና አገልግሎት ሰጪ ተቋማት በአቅርቦቱ መስክ እና የግል እና የህዝብ ተጠቃሚዎች ደግሞ የፍላጎቱን መስክ እድገት ያሳያሉ።

መንግስትም የዕድገት ለዉጥ ትግበራዉን በማፍጠን እና ቀጣይነት ያለዉን እድገት በማስፋፋት በ 2035 እ.አ.አ ከመካከለኛ ዕድገት ላይ ካሉ ሀገራት ለማሰለፍ እየሰራ ይገኛል። ይሄንን እድገትም ለማፋጠን መንግስት መሰረተ ልማቶችን ከህዝብና ከግል ኢንቬስተሮችም ጋር በትብብር ጉዞዉን ጀምሮ ቆይቷል። አሁን ላይ ያለዉን የህዝብ ቁጥር ስናይ ወደ 120 ሚሊዮን ከሚጠጋዉ ህዝብ ትልቁን ድርሻ የያዘዉም ወጣቱ ሲሆን እነዚህም ከተሰራበት የህዝብ ቁጥሩም ሆነ የወጣቱ ቁጥር መልካም እድል የሚሆንበት ሁኔታ አለ። እነዚህ ሁሉ ወጣቶች፣ የጤና፣ የቤት፣ የትምህርት እና የስራ ዕድል ስለሚፈልጉ ይሄ ጫና የሚመስለዉን ጉዳይ ወደ እድል መለወጥ ተገቢ ነዉ።

ከሚሌኒዬሙ የእድገት እቅድ ኢትዮጵያ በ እናቶች እና ህጻናት ሞት ከፍተኛ መቀነስ ስራ ቢሰራም አሁንም ቢሆን ብዙ ስራ ይጠብቀናል። በቅርብ በወጣዉ የጤና ሚኒስቴር መረጃ መሰረት 60 በመቶ ሞት ከእናቶች ህጻናት እና ተላላፊ በሽታዎች ቢሆንም 30 በመቶዉ ደግሞ ከማይተላለፉ በሽታዎች ጋር ይያያዛል።
የትምህርት ጥራትንም ብናየዉ በጤናዉ ትምህርት ዘርፍ የጥራቱ ጉዳይም አሳሳቢ ደረጃ ላይ ደርሷል። የትላልቅ ትምህርት ተቋማቶቻችንም ዉስጥ ገብተዉ በብዙ የሀገር ኢንቬስትሜንት የሚማሩ ምሁራንም የተሻለ ነገር ፍለጋ ከሃገር መሰደድ ላይ ይገኛሉ። ሀገር ዉስጥ የቀሩትም በህብረት ያላቸዉን እዉቀት፣ ጊዜ እና ገንዘብ አሰባስበዉ ወይም ከሌሎች ባለ ሃብቶች ጋር በህብረት በመሆን በሰፊዉ የመስራት ባህሉ ብዙም አይታይም።

ከላይ የተጠቀሱት ችግሮችን እንደ አጋጣሚ በመጠቀም የተማሩ እና ትዉልደ ኢትዮጵያዉያን የሆኑ ሰዎች በአንድነት በረጅም አመታት እቅድ ቢሰሩበት ፍሬያማ ዕዉቀት እና የስራ ዕድል ለወጣቱ፣ ለህብረተሰባችንም ደዌ መፍትሄ ብሎም በአንድነት እዉቀትን እና ገንዘብን አንድ ላይ ለሚሰሩበት ኢትዮጵያዉያን እርካታ፣ ክብር እና ሃብትንም ያጎናጽፋቸዋል።
በአንድነት ያለንን አሰባስበን መንግስትንም በጥናት በማሳመን መስተካከል ያለባቸዉን ጉዳዮች በማስተካከል ህዝባችንን ጠቅመን እኛም መጠቀም እንችላለን። በሀገራችን ያሉትን የመልካም አጋጣሚዎች መካከል፡-

የወደፊቱ የአለማችን ሀብት ምንጭ የሚባለዉ መረጃ ሲሆን በዚህ ላይ በሀገራችን እምብዛም አልተሰራም። ከላይ ያሉ የጤና ችግሮች በዘላቂነት ለመፍታት፣ ከመፍትሄዉ የሚገኘዉን ገቢ ለማግኘት እና ዉጭ ምንዛሬ ለማትረፍ የጤና ቴክኖሎጂ መሠረተ ልማቶች ላይ መስራቱ ተቀዳሚ ነዉ። የጤናዉ የቴክኖሎጂ መሰረተ ልማት በሀገራችን ምንም ያልተሰራበት በሚባል ደረጃ ላይ ያለ ሲሆን አብዛኛዎቹም በዕርዳታ ድርጅቶች ላይ የተደገፉ ከመሆናቸዉም በላይ ዘላቂ የሆነ ሀገራዊ የጤና ቴክኖሎጂ ህልም ያላቸዉ ባለመሆናቸዉ የጤና መረጃዎችን ጥቅም ላይ ለማዋል አልተቻለም። ስለዚህ በተለያዩ ቦታዎች ያሉ ትዉልደ ኢትዮጵያዉያን አለም አቀፍ የእውቀት አቅም ኖሯቸዉ ካልተጠቀሙ ኢትዮጵያዉያን ባለሙያዎች ጋር በመሆን መስራት የሚችሉበት መስክ ነዉ። በአንድነት ያላቸዉን በማሳየት መንግስትም ለዚህ ከመደበዉ በጀት ድጋፍ በማግኘት በቡድን ራስንም ሀገርንም መለወጥ ይቻላል።

አብዛኞቹ ህዝባችን የሚሞተዉ በጤና ግንዛቤ ማነስ እና የጤና አገልግሎት እጦት በመሆኑ የመረጃዉ ቴክኖሎጂ መኖር፣ ስራ አተዉ ያሉ የተማሩ ወጣት ሃይልን በመጠቀም እና በማሰልጠን፣ የስራዉም ሆነ የሃብቱ አካል በማድረግ በፒራሚዳል ስኪም ኢንሹራንም ሆነ መረጃን ማሰራጭት የሚቻልበትም ሁኔታ አለ።

የጤናዉን ትምህርት ብናይም አለም አቀፍ ጥራቱን የጠበቀ የጤና ትምህርት መስጫ ተቋማት አንድም ያለመኖርን እንደ እድል በመቁጠር በጋራ በዚያም ዘርፍ ኢንቬስት በማድረግ መስራት ይቻላል። ለዚህ ደግሞ አመቺ ሁኔታ ከሚፈጥሩ ጉዳዮች መካከል በሃገራችን ከፍያ እስኬል አለም አቀፍ ተወዳዳሪ የሆኑትን እና በተለያዩ አለም አቀፍ ተቋማት የተማሩ ስፔሺያሊስት ሃኪሞቻችንን በአካል በኢትዮጵያ ሌሎችንም ደግሞ ካሉበት በ ቴክኖሎጂ በማሳተፍ የተማረ ሃይል በማምረት ለአለም አቀፍ ገበያ ማቅረብም ሆነ ለሀገር ማብቃትም ይቻላል።

አብረን በጋራ በመሆን ችግሮቻችንን በመጠቀም የመፍትሄም፣ የሃብትም ምንጭ እናድርጋቸዉ! የችግራችን ምንጭ አብሮ ያለመሮጥ፣ አብሮ ያለማሰብ ሲሆን፡ ድር ቢያብር አንበሳ ያስር ነዉና፤ ይብቃን አብረን አንሁን፣ አብረን እናስብ ያለንን አንስተን ችግር እንፍታ የመፍትሄም ምንጭ እናድረገዉ። ይሄ ስራ የሃብት ምንጭነት ብቻ ሳይሆን የዞሮ መግቢያችን ቤት ስራ ጉዳይ ስለሆነ እንበርታ።

ዋቢ ጽሁፎች
1. Ethiopia Growth and Transformation Plan II and Ministry of Health, Addis Ababa 2016: Investment Process in Ethiopia’s Health Sector. By National Planning Commission
2. Central Statistical Agency/CSA/Ethiopia and ICF. Ethiopia Demographic and Health Survey 2016. Addis Ababa, Ethiopia, and Rockville Maryland, US: CSA and ICF. 2016.
3. Health Systems 2020: Health Care Financing Reform in Ethiopia: Improving Quality and Equity.
https://www.hfgproject.org/wp-content/uploads/2015/02/Ethiopia_Health_Care_Reform_Brief1.pdf
4. Health Sector Development Programme IV, 2010/11–2014/15. Final draft (pdf 780.81kb). Addis Ababa, Government of Ethiopia, Federal Ministry of Health, 2010

በዶ/ር ተመስገን እንዳለዉ
(MD, Systems Developer, CSMM, MBA, MSc cand, CEO Hakim Consult)

Continue Reading

ቴክኖሎጂ

አሁን ባለንበት ዘመን ለዘላቂ ሀገራዊ ጉዳይ ራድዮ ያለው ሚና

Published

on

featured

ሰዎች የራድዮ የመገናኛ ዘዴን በየትኛውም ሁኔታ ውስጥ ሆነው የሚሰሙት የመገናኛ ዘዴ ነው።የራድዮ የመገናኛ ዜዴ ለአንድ ሀገር እድገት እና ብልግና እጅግ ጠቃሚ ድልድይ ነው ህዝብን ከህዝብ ያቀራርባል መንግስትንም ከህዝብ ያገናኛል መረጃ ያደርሳል። ስለዚህ መገናኛ ብዙሃን የህዝብን ችግር ለይቶ በማውጣት ለመንግስት በማድረስ እና ችግሩ እንዲፈታ በማድረግ ትልቅ ሚና ይጫወታል።የራድዮ መገኛ ብዙሃን ነፃና ገለልተኛ ሆኖ ህብረተሰቡን ማገልገል ይጠበቅበታል እንዲሁም ተጠሪነታቸው ለእውነት እና ለሀቅ ከሆነ ብዙ ነገሮችን መቀየር ይቻላል።

በተለይ የህዝብን ጥያቄ እየተከታተለ ለሚመለከተው አካል ከማድረስ አንፃር ትኩረት ሊያደርግበት  የሚገባ ጉዳይ ይሆናል።ምክንያቱም ራድዮ ድልድይ ሲሆን የሰላም መሸጋገርያ፣የመፍትሔ ማፍለቂያ ፣የሀሳብ ማስታረቂያ የተሸፈነውን  መግለጫ ይሆናልና።

ሀገራዊ ጉዳዮችን ከማንሳት አንፃር ተግተው ሊሰሩ ይገባዋል ራድዮ መቆም ያለበት ለሀገር ነው።ከሀገር በላይ ምንም ነገር የለም ሀገር ስትኖር ነው ሁሉ የሚያምረው ስለዚህ ሀገራዊ ጉዳይ በስፋት መታየትና መዳሰስ መሰራት ይኖርባቸዋል። ሀገር ማለት ህዝብ ነው ስለዚህ የህዝብን የልብ ትርታ ምን እንደሆነ አስቀድሞ በመረዳት ለህዝብ የሚጠቅሙ፣ የሚያግዙ ጉዳዮችን ላይ አበክሮ መስራት ያስፈልጋል። የህብረተሰቡን ችግር ነጥሎ በማውጣት የሚበጁ መፍትሔዎችን መጠቆም አቅጣጫዎች ማስመልከት የሚዲያ ተቀዳሚ ተግባሩ ሊሆን ይገባል።

ሁሉም ነገር እንዳጠቃቀማችን ነውና ሚድያውን በአግባቡ ከተጠቀምነው ሀገርን መለወጫ ማሻሻያ ምርጥ መሳርያ ማድረግ ይቻላል። የሀገር ሰላምን ከማስፈን አኳያ የተጣሩና የተረጋገጡ መረጃዎችን ለህብረተሰቡ ከማቅረብ አንፃር መትጋት ያስፈልጋል። ሰላም ከሌለ ምንም ሊኖር አይችልም የራድዮ የመገናኛ ብዙሃን ለሰላም ቅድሚያ ሊሰጡ ይገባቸዋል። ስለ ሰላም መወያየት ስለ ሰላም መነጋገር ያስፈልጋቸዋል።

ሰላምን እንዴት ማስፈን እንደሚቻል ማሰላሰል ይጠበቅባቸዋል ከዚህ ጋርም በተያያዘ ሀገር በቀል የግጭት አፈታት ዘዴዎችን ለማህበረሰቡ በማስተማር መረጃ መሰጠት የዚሁ ሚዲያ ተቀዳሚ ተግባሩ ሊሆን ይገባዋል።በሀገራችን ቀደምት ሀገር በቀል የግጭት አፈታት ዘዴዎች እንዳሉ እሙን ነው ስለዚህ እነዚህን ጥበቦች ወደ ማህበረሰቡ አምጥቶ ከዘመኑ እና ከጊዜው ጋር በማስታረቅና በማቀራረብ ልንጠቀምበት ያስፈልጋል።

ኢትዮጵያ የብዝሀ ሀብት ባለቤት ናት ብዙ የኔ የምትላቸው በጎ በጎ የሆኑ ባህል፣ ወግ፣ እሴትና ማንነት ያላት ድንቅ ሀገር ናት። ስለዚህ እነዚህን ወርቃማ እድሎች እንዴት መጠቀም እንዳለብን የተለያዩ ጥናቶችን አድርጎ ማህበረሰቡን ልናግዘው ይገባል። በተጨማሪም የሰላምን ዋጋ በተግባር ለህብረተሰቡ ግንዛቤ በማስጨበጥ አቅጣጫ መጠቆም እና ማስረፃ ጠቃሚ ይሆናል።

ራድዮ ለሀገራዊ ሰላም ያለው አስተዋፅኦ እጅግ በጣም ሰፊ ነው። ምክንያቱም ራድዮ ብዙዎች ይሰሙታ… ከህፃናት እስከ አዋቂ፣ ከገጠር እስከ ከተማ በሁሉም እድሜ ክልል ውስጥ ያሉ ሰዎች ያደምጡታል ስለዚህ ህብረተሰቡን ለመጥቀም ትልቅ ሀብት ነው።ትልቅ መሳርያ ነው።

መገናኛ ብዙሃን ማህበረሰብን ከማህበረሰብ የማስተሳሰር ሚናው ከፍተኛ ነው የህብረተሰቡን አብሮ የመኖር እሴት ማጠናከርና ማስጠበቅ ሚዲያው ትልቅ ድርሻ ሊኖረው ይገባል።ኢትዮጵያ የብዙ ህዝብ ባለቤት ናት በህዝቦቿ መካከል ደግሞ ከጥንትም የነበረ አብሮ የመኖር ሚስጢር ነበራት። አሁንም ይህንን አብሮ የመኖር ሚስጢር እንዴት አድርገን ማስቀጠልና ማስኬድ እንዳለብን ልንወያይና ልንመረምር ያስፈልጋል።

ጠቃሚ የሚባሉ የህዝብ ሀሳቦችን በመቀበልና ለብዙዎች በማስተጋባት ትልቁን ሀላፊነት ልንወስድ ይገባል። የብዙ ብሔርና ብሔረሰቦች ስብስብ የሆነችው ሀገራችን ኢትዮጵያ ለዘመናት የተሻገሩ ብዙ አብሮ የመኖር ጥበቦች ያላት ሀገር ናት።የራድዮ መገናኛ ብዙሃን አብሮነትን ከማጠናከር አኳያ ብዙ ስራዎችን በመስራት እውነትን በመግለጥ እና ሀሰትን በመቅበር ታሪክን ሊሰራ ግድ ይለዋል።

አንዳንድ ለዘመናት በአፈ ታሪክ ሲወራረዱ የመጡ በጎ ያልሆኑ አብሮ የመኖር ሚስጢርን ሊፈታተኑና ሊያቀጭጩ የሚችሉ ጉዳዮችን አብዝቶ ከመቃወምና ከማስቀረት አነነፃር የሚድያው ሀላፊነት የትየለሌ ነው።ሀገር የምትቆመው በሰዎች መልካካም ሀሳብ ነው እናም የመገናኛ ብዙሃን መልካም መልካም ሀሳቦችን ሸጋ ሸጋ ረቂቆችን በማጥናትና በማሰናሰን ለህብረተሰቡ መትጋት ይኖርበታል። መገናኛ ብዙሃን ለሃገር ሰላምና አንድነት የማይተካ ሚና አላቸው።

በተለይ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ የሚያጠነጥኑ ፕሮግራሞች መብዛትና መበራከት አለባቸው ያን ጊዜ ማህበረሰቡ ለሀገር ሰላምና ደህንነት ዘብ ይቆማል።

ቤንኦን ጌታቸው

Continue Reading

ቴክኖሎጂ

ሶሻል ሚድያ ለልጆች መከልከል የለበትም

Published

on

featured

በብዛት ሶሻል ሚድያን የሚያጥላሉት ባለሙያዎች ራሳቸዉ ሶሻል ሚድያን አብረዉ የፈበረኩ እና አቅማቸዉ ከአሰሪዎቻቸዉ አልመጣጠን ሲል ሚስጥር አወጣን በማለት የሰሩት ዶኩሜንታሪ “The Social Dilemma” ሲሆን ሌሎችም የነዚህን ሰዎች ሃሳብ የሚያራግቡት ትልልቆቹ ሚድያዎች በ ፌስቡክ ስለተበለጡ እና ፌስቡክ ብዙ ተከታዮቻቸዉ ላይ ያለ ክፍያ መድረስ እንዳይችሉ ማድረግ ከጀመረ በኋላ እንደ ዘመቻ በጋራ የማጥላላት ዘመቻ የተያያዙ ነዉ የሚመስለዉ።

ሶሻል ሚድያ መጠቀምን በተለይ ፌስቡክ ማለትን ከ ዕለት ተዕለት ኖሮ ጋር ብናመሳስለዉ፡-  ፌስቡክ ዉስጥ መግባትን ከቤት ዉጭ እንደመዉጣት ብናየዉ፣ ፖስት ማድረግ ማለት የምንነጋገረዉ ንግግር ሲሆን ኮሜንት ደግሞ አጠገባችን ላለዉ እና ለሚያወራወራዉ ሰዉ የምንመልሰዉ መልስ አድርገን ብንወስደዉ።

በዚህ አካላዊ በሆነዉ ግኑኝነታችን ምን እንደምንሰማ እና ከማን ጋር እንደምናወራ እንደምንጠነቀቀዉ ሁሉ በሶሻል ሚድያዉም እንዲሁ እንዴት መጠንቀቅ እንዳለብን ለልጆቻችን ከማስተማር ዉጪ ሙሉ በሙሉ መከልከሉ ብዙም የሚያዋጣ ዉሳኔ ላይሆን ይችላል።

ሶሻል ሚድያን ልጆች እንዳይጠቀሙ መከልከል የምንችልበት ጊዜ ላይ አይደለንም ያለ ነዉ። የአሁን ጊዜ ልጆች ሶሻል ሚዲያን የሚጠቀሙት የአካላዊ ግኑኝነቱ ቀጣይነት አድርገዉ ስለሆነ ይሄንን ሁኔታ መከልከሉ ለአዕምሯቸዉ እድገትም ቢሆን እጅጉን ጉዳት ሊያደርስ ይችላል።

የሶሻል ሚድያ ጥቅሞች፡-

  1. ሶሻል ሚድያ የዘመኑ ልጆች ትልቁ መዝናኛ፣ ከሌሎች ሰዎች መገናኛ፣ ፍላጎታቸዉን ማካፈያ፣ ሌሎችንም ሰዎች ማወቂያ እና መግባቢያም ጭምር ነዉ። በተለይ ጉርምስና ላይ ላሉ ከጓደኞቻቸዉ ጋር መግባቢያ ቦታም ጭምር ነዉ።
  2. ልጆች ከ ሶሻል ሚድያ ሊያገኟቸዉ የሚችሏቸዉ ጥቅሞች መካከል፡- ሚድያዉ እንዴት እንደሚሰራ ከ አዕምሯቸዉ ጋር እንዲላመድ ማድረግ እና በ አግባቡ እንዴት መጠቀም እንዳለባበቸዉ መማር እና ራሳቸዉን ሳይጎዱ እንዲጠቀሙ እንዲያዉቁ ይረዳቸዋል።
  3. ከሌሎች ጋር በመተባበር የሆነን ነገር ለመማማር ይጠቅማል፣ ትምህርታዊ ነገሮችንም ይከፋፈላሉ፡
  4. ከሌሎች ጋር መሆኑ ብቸኝነት እንዳይሰማቸዉ ሊያደርጋቸዉ ይችላል።

የሶሻል ሚድያ አሳሳቢ ጎኖች፡-

  1. ልጆች አላስፈላጊ የሆነን ይዘት ያለዉ መረጃ ሊያዩ ይችላሉ
  2. ትክክል ነዉ እንተርኔት ላይ የወጣ ሰዉ በሙሉ ከፈለገ እንዲህ አይነት ጉዳት የሚያደርሱ ነገሮችን ማያይበት ሁኔታ የለም፣ ነገር ግን እንዴት ከዚህ ራሳቸዉን መጠበቅ እንዳለባቸዉ ማስተማሩ፡ ከመከልከሉ ያዋጣል።
  3. ሶሻል ሚድያ ላይ ልጆች አላስፈላጊ የሆነን እና ሰዉነትን የሚያጋልጥ ፎቶ ሊለቁ ይችላሉ
  4. የተለያዩ የግል መረጃዎችን ለምሳሌ ስልክ ቁጥራቸዉን፣ የትዉልድ ዘናቸዉን ወዘተ ለማያዉቁት ሰዉ ማጋራት ወዘተ
  5. ለተለያዩ ማስታወቂያዎች ይጋለጣሉ

ሶሻል ሚድያን መከልከል ስለማንችል፡

  1. ስለትክክለኛዉ አጠቃቀም መማማር / የወደፊቱ እዉነታ ስለሆነ ቤተሰብ እራሱ በራሱ ከመምከር ይልቅ እንዴት በትክክል መጠቀም እንዳለባቸዉ በባለሙያዎች ትምህርት እንዲወስዱ ማድረግ/
  2. በሶሻል ሚድያ እንዴት ከሰዎች ጋር መግባባት እንዳለባቸዉ ማስተማር
  3. ልጆቻቸዉን አደጋ ላይ ሊጥል ስለሚችል ነገር ክትትል ማድረግ
  4. የተለያዩ መረጃዎችን የሚጠይቋቸዉ ሰዎችን እና ጓደኞቻቸዉን እንዲለዩ እና በደምብ እንዲያዉቁ ማድረግ
  5. እያንዳንዱ ልጆቻችን የሚጠቀሙትን የሶሻል ሚድያ አይነት እንዴት እንደሚሰራ በአግባቡ ማጥናት
  6. አላስፈላጊ እና ጎጂ የሆኑ ይዘቶችን እራሳቸዉ እየለዩ መጠንቀቅ እንዳለባቸዉ ማስተማር
  7. የተለያዩ ግላዊነት እና መረጃዎቻቸዉን እንዴት መጠበቅ እንዳለባቸዉ ማስተማር እና መከታተል

እነዚህን ከላይ ያሉትን ነገሮች በማድረግ ልጆቻችን በአግባቡ መጠቀም እንዲችሉ ከመርዳት ዉጪ ሙሉ በሙሉ እንከለክላለን ማለት ወይም እድሜአቸዉ ከፍ ሲል ይጠቀሙ ማለት ሁለቱም የራሳቸዉ የሆነ ጉዳት አላቸዉና፣ ነገሩ ህልም ተፈርቶ ሳይተኛ አይታደርምና ነገሩ እየተማሩ ቢያድጉ መልካም ነዉ።

ሌላዉ ነገር ብዙ ጊዜ አንድ ስለ ሶሻል ሚድያ የሚያወሩ እድሜያቸዉ ገፋ ያሉ ሰዎች ስለ የሶሻል ሚድያ በነሱ አይን እና በአሁን ዘመን ልጆች አይን እንድ እንዳይደለ መረዳት መቻል አለባቸዉ። ይሄም ማለት የዘመኑ ልጆች ጭንቅላት እንጅጉን ፈጣን ስለሆነ ብዙ ነገሮች በአንዴ ሲያስሱ ወላጆች ሊጭንቃቸዉ ይችላል። ይሄም የሆነበት ልጆችን ለነገዉ የጭንቅላት እድገት እንዲያዘጋጃቸዉ አዕምሮአቸዉ እንደሰጣቸዉ አቅም ማየቱ እና መደገፍ እንጂ አስሮ ለማስቀመጥ ያለመታገሉ መልካም ነዉ።

ካደጉ በኋላ ይጠቀሙ እንዳንልም መቼም ቢሆን ለማንም ሶሻል ሚዲያ የራሱ ጉዳትም ጥቅምም ስላለዉ እየተማሩ ቢያድጉበት አና ራሳቸዉን ቢጠብቁ ይሻላል እላለሁ።

በእኔ አመለካከት እይታችንን የሚወስነዉ ያደረግነዉ “መነጽር” በመሆኑ የልጆቹን “መነጽር” / አመለካከት እና እዉቀት ማስተካከሉ ሳይጎዱ እንዲጠቀሙ ያስችላል ብዬ አስባለሁ
የሬሴን የግል ሁኔታ ሳካፍል ሶሻል ሚድያን በተለይ ፌስቡክን ከ12 አመት በፊት ጀምሮ ተጠቅሜዋለሁ እጅጉን በጣም እንዳደገ ይሰማኛል፡ በዚያም ላይ የነገዉ የመግባቢያችን መንገድ ከመሆን ምንም የሚከለክለዉ ነገር አይታየኝም። ግዜዬን የማጠፋበትን ነገር የምወስነዉ እኔ ነኝ እንጂ ሌላ ዉጫዊ ነገር አይደለም።  ነገር ግን ስለ ፌስቡክ ወይም ሶሻል ሚድያዎች አጠቃቀም በስርዓት ከተማርኩ በኋላ ስለተጠቀምኩ እንዴት ሳልጎዳ እንድጠቀም አስችሎኛል። ስለዚህም ልጆቻችንን ጭራሽ ከመከልከል እንዴት መጠቀም እንዳለብን ቤተሰብም እነሱም በዕዉቀት ብናደርገዉ የተሻለ ነዉ።

ዶክተር ተመስገን እንዳለዉ

Continue Reading

በብዛት የተነበቡ